ሞዛምቢክ አየር መንገዷን ለመታደግ የኢትዮጵያን ሙያዊ ድጋፍ መፈለጓ ተገለፀ

ሰብስክራይብ

ሞዛምቢክ አየር መንገዷን ለመታደግ የኢትዮጵያን ሙያዊ ድጋፍ መፈለጓ ተገለፀ

የሞዛምቢክ ብሔራዊ አየር መንገድ እያጋጠመው ያለውን ከፍተኛ ኪሳራ እና የአሠራር ችግር ለመቅረፍ የኢትዮጵያን አየር መንገድ ልምድና እገዛ ለመጠየቅ መወሰኑ ተገልጿል።

‍ የአጋርነት ጥያቄው ሞዛምቢክ አብራሪዎቿን በኢትዮጵያ አየር መንገድ የልህቀት ማዕከል ለማሠልጠን ያላትን ፍላጎት እና ከከፍተኛ ዕዳ እና ኪሳራ ለመውጣት የአሠራር ተሞክሮ መቅሰምን ያካተተ መሆኑን የሀገሪቱ መገናኛ ብዙሃን ዘግቧል።

"ኢትዮጵያ በአፍሪካ ግዙፉ አየር መንገድ አላት፤ እኛ ደግሞ የራሳችንን አየር መንገድ የማነቃቃት ህልም አለን። ካለ ምንም ተነስተው እዚህ ደረጃ ላይ በመድረሳቸው ከእነሱ በላይ የምንማርበት የተሻለ ቦታ የለም" ሲሉ በኢትዮጵያ የሞዛምቢክ አምባሳደር ኑኖ ቶማስ ተናግረዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0