በሩሲያ ላይ የኒውክሌር ጥቃት ለመሰንዘር ማሰብ "በእሳት መጫወት" ነው - ሶሪያዊ ባለሙያ
18:18 25.02.2026 (የተሻሻለ: 18:24 25.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሩሲያ ላይ የኒውክሌር ጥቃት ለመሰንዘር ማሰብ "በእሳት መጫወት" ነው - ሶሪያዊ ባለሙያ
የሩሲያ የደህንነት ተቋም በቅርቡ ፈረንሳይ እና እንግሊዝ ለዩክሬን የኒውክሌር መሣሪያዎችን ለማቅረብ እያጤኑ መሆኑን መግለጹ "ተስፋ መቁረጣቸውን" እንደሚያሳይ በሞስኮ የጄ.ኤስ.ኤም የምርምር ማዕከል ዳይሬክተር አሰፍ ሙልሂም ለስፑትኒክ ገልጸዋል።
ፓሪስ እና ለንደን "እውነተኛውን የኃይል ሚዛን በመዘንጋት ለማስፈራራት እየሞከሩ ነው" ሲሉ አክለዋል።
ሙልሂም አክለውም፤ ከአውሮፓ መሪዎች ለሚሰነዘር እንዲህ ዓይነት "ተስፋ የቆረጠ" ጠብ አጫሪነት የሞስኮ ምላሽ "አደገኛ" ይሆናል ሲሉ በግልጽ አስጠንቅቀዋል።
ቭላድሚር ፑቲን ከብሪክስ ሚዲያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ (ከላይ ያለውን ቪዲዮ ይመልከቱ) ሩሲያ በማንኛውም ሁኔታ ዩክሬን የኒውክሌር መሣሪያ እንድታገኝ እንደማትፈቅድ አስቀድመው ማስጠንቀቃቸው ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X