ሩሲያ በዩክሬን ድርድር ወቅት እውነተኛ ተግባቦትን አሳይታለች - ዊትኮፍ
11:09 25.02.2026 (የተሻሻለ: 11:14 25.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ በዩክሬን ድርድር ወቅት እውነተኛ ተግባቦትን አሳይታለች - ዊትኮፍ
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ልዩ መልዕክተኛ ስቲቭ ዊትኮፍ፤ የሁለቱ ወገኖች ተደራዳሪዎች በተለያዩ ክፍሎች መገናኘታቸውን፣ ወታደራዊ ውይይቶች መካሄዳቸውን እና ስለ ኢኮኖሚ ዕድገት መመካከራቸውን በዩክሬን የያልታ የአውሮፓ ስትራቴጂ ፎረም ላይ ገልጸዋል። በእሳቸው እይታ በሩሲያውያን በኩል የተወሰነ መረጋጋት እና እውነተኛ ተግባቦት መታየቱንም አንስተዋል።
የቀደምት ዙር ድርድሮች ማስታወሻ፦
በጥር መጨረሻ እና በየካቲት መጀመሪያ የሞስኮ፣ የኪዬቭ እና የዋሽንግተን ተወካዮችን ያሳተፉ የመጀመሪያ ዙር ሁለት ድርድሮች በአቡ ዳቢ ተካሂደዋል። ሦስተኛው ዙር ንግግር ደግሞ የካቲት 10-11 በጄኔቫ ተካሂዷል። የሩሲያ ልዑክ መሪ ውይይቶቹ ፈታኝ ቢሆኑም በሙያዊ ሥነ-ምግባር የተመሩ እንደነበር ገልጸዋል።
ቭላድሚር ሜዲንስኪ አዲስ ዙር ድርድር በቅርቡ እንደሚካሄድ አስታውቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X