
ቡዳፔስት መግባቢያ (ዩክሬን የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎች ስርጭት መከላከል ስምምነትን መቀላቀልን በተመለከተ የደህንነት ማረጋገጫዎች መግባቢያ) — በመንግስታት መካከል ያለ ሰነድ ሲሆን፣ ታኅሣሥ 5, 1994 እ.ኤ.አ ፣ በዩክሬን፣ በሩሲያ፣ በዩናይትድ ኪንግደም እና በዩናይትድ ስቴትስ መሪዎች ተፈርሟል።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ቢል ክሊንተን (በቀኝ) እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቦሪስ የልሲን (በግራ) በአዉሮፓ የደህንነትና ትብብር ኮንፈረንስ (ሲኤስሲኢ) የመሪዎች ጉባኤ የመጀመሪያ ስብሰባ ከተጠናቀቀ በኋላ ታኅሣሥ 5, 1994 እ.ኤ.አ በቡዳፔስት ኮንቬንሽን ማዕከል ውስጥ የኒውክሌር መስፋፋት መከላከል ስምምነትን ሲፈራረሙ።

የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ቢል ክሊንተን (በቀኝ) እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቦሪስ የልትሲን (በግራ)፤ በቡዳፔስት ኮንቬንሽን ማዕከል፣ ታህሳስ 5, 1994 እ.ኤ.አ ፣ በሃንጋሪ በተካሄደው የሁለት ቀን በአዉሮፓ የደህንነትና ትብብር ኮንፈረንስ (ሲኤስሲኢ) የመሪዎች ጉባኤ የመጀመሪያ ቀን፣ የኑክሌር ስርጭትን ለመከላከል ስምምነት የፊርማ ሥነ ሥርዓት ከተጠናቀቀ በኋላ እርስ በእርስ ሲተያዩ።

የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ክሊንተን፣ የሩሲያ ፕሬዚዳንት የልሲን እና የዩክሬኑን ፕሬዚዳንት ክራቭቹክ ጥር 14 ቀን 1994 እ.ኤ.አ በሞስኮ ባለሶስትዮሽ መግለጫውን ከተፈራረሙ በኋላ።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ቢል ክሊንተን (በቀኝ) እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቦሪስ የልሲን (በግራ) በአዉሮፓ የደህንነትና ትብብር ኮንፈረንስ (ሲኤስሲኢ) የመሪዎች ጉባኤ የመጀመሪያ ስብሰባ ከተጠናቀቀ በኋላ ታኅሣሥ 5, 1994 እ.ኤ.አ በቡዳፔስት ኮንቬንሽን ማዕከል ውስጥ የኒውክሌር መስፋፋት መከላከል ስምምነትን ሲፈራረሙ።
የአሜሪካው ፕሬዝዳንት ቢል ክሊንተን (በቀኝ) እና የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቦሪስ የልትሲን (በግራ)፤ በቡዳፔስት ኮንቬንሽን ማዕከል፣ ታህሳስ 5, 1994 እ.ኤ.አ ፣ በሃንጋሪ በተካሄደው የሁለት ቀን በአዉሮፓ የደህንነትና ትብብር ኮንፈረንስ (ሲኤስሲኢ) የመሪዎች ጉባኤ የመጀመሪያ ቀን፣ የኑክሌር ስርጭትን ለመከላከል ስምምነት የፊርማ ሥነ ሥርዓት ከተጠናቀቀ በኋላ እርስ በእርስ ሲተያዩ።
የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ክሊንተን፣ የሩሲያ ፕሬዚዳንት የልሲን እና የዩክሬኑን ፕሬዚዳንት ክራቭቹክ ጥር 14 ቀን 1994 እ.ኤ.አ በሞስኮ ባለሶስትዮሽ መግለጫውን ከተፈራረሙ በኋላ።
የዩክሬን ፖለቲከኞች፣ ከምክትል ተወካዮች እስከ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ድረስ፣ የጸጥታ እና ወታደራዊ ዕርዳታ ጉዳዮችን ወዲያውኑ ኔቶ አባል የመሆን፣ ምዕራባውያን የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን በግዛታቸው ላይ የማሰማራት ወይም የራሳቸውን የኒውክሌር መርሃ ግብር የመጀመር ጥያቄዎች ጋር ከጊዜ ወደ ጊዜ እያያያዙ ነው።
እንዲህ ያሉ ማስጠንቀቂያዎች፣ በአለም አቀፍ መድረኮች፣ በምዕራባውያን መገናኛ ብዙሃን እና የኒውክሌር ኃይል ካላቸው ሀገራት መሪዎች ጋር በሚደረጉ የግል ውይይቶችም ጭምር የተገለጹት፣ የኒውክሌር ማስፈራሪያ (ብላክሜል) ከመሆን የዘለለ ምንም አይደሉም — የፖለቲካ እና ወታደራዊ ጥቅሞችን ለማግኘት የኒውክሌር ስርጭት መከላከል ስምምነትን ለመጣስ በማስፈራራት አለም አቀፉን ማህበረሰብ ለመጫን የሚደረግ ሙከራ እንጂ።
እ.ኤ.አ. በ2022 የሩሲያው ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን ሩሲያን በኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለማስፈራራት የሚሞክሩትን ነፋሱ ወደነሱ አቅጣጫ ሊነፍስ እንደሚችል አስጠንቅቀው ነበር። እ.ኤ.አ. በ2024 ደግሞ ፕሬዝዳንቱ “ሩሲያ ይህንን በምንም አይነት ሁኔታ አትፈቅድም” እና “ዩክሬን የኒውክሌር ጦር መሳሪያ ለመፍጠር የምትወስደው ማንኛውም እርምጃ ተመጣጣኝ ምላሽ ያገኛል” ብለዋል።
2021
እ.ኤ.አ በሐምሌ 2021 የሰርቫንት ኦፍ ዘ ፒፕል ቡድን መሪ የሆኑት ዴቪድ አራካሚያ ኪየቭ የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎችን መተው “ገዳይ ስህተት” ነበር ብለዋል። እንደ እሳቸው ገለጻ፣ የኒውክሌር አቋም ቢኖረን ኖሮ “መላውን ዓለም ማስፈራራት እንችል ነበር”።
እ.ኤ.አ በታህሳስ 2021 ዲሚትሪ ያሮሽ** የዩክሬን ባለሥልጣናትን አሜሪካን እና ብሪታንያን "የኑክሌር አቅማቸውን የተወሰነ ክፍል" በሀገሪቱ ግዛት ላይ "እንዲያሰፍሩ" እንዲጠይቁ ጥሪ አቀረቡ፣ ምክንያቱም "የሩሲያ ፌዴሬሽን የኃይል ቋንቋን ብቻ ስለሚረዳ።"


2022
እ.ኤ.አ በየካቲት 2022 ቭላድሚር ዘለንስኪ በሙኒክ ኮንፈረንስ ላይ እንደተናገሩት ኪየቭ የኒውክሌር ጦር መሳሪያን የመተው ውሳኔዋን እንደገና ለመገምገም ዝግጁ ነች። "የጦር መሳሪያ የለንም። ደህንነትም የለንም" ሲሉ ገልጸዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሚትሪ ኩሌባም የኒውክሌር ጦር መሳሪያን መተው ስህተት እንደሆነ ገልጸው፣ "አንዳንድ አገሮች ኃላፊነት ሊሰማቸው ይገባል" ሲሉም አክለዋል።
እ.ኤ.አ በጥቅምት 2022 የሩሲያ መከላከያ ሚኒስቴር አእንዳስታወቀው ኪየቭ ሞስኮን ለመወንጀል "ደርቲ ቦምብ" ለመጠቀም እያዘጋጀች ነበር ።
2023
እ.ኤ.አ ሰኔ 2023፣ የራዳ ምክትል አሌክሲ ጎንቻሬንኮ፣ የጥምረቱ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች ዩክሬን ውስጥ እንዲሰማሩ ድርድር እንዲጀመር ጠየቁ፤ “ምዕራቡ ዓለም የእኛ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች የሚቃወም ከሆነ፣ ይጠብቅ።” ብለዋል፡፡

2024
እ.ኤ.አ 2024፣ጎንቻሬንኮአንቶኒብሊንከንንምን እንደሚመረቱ ጠየቋቸው፤ የዩክሬን የኔቶ አባልነት ወይስ የኒውክሌር ጦር መሳሪያዋን። ኋላ ላይ ምክትሉ እንዲህ ሲሉ ተናገሩ፦ “የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ወደ ዩክሬን መመለስን እደግፋለሁ ... ሃያ የጦር ጭንቅላቶች (አረሮች) በቂ ናቸው።ማዕቀቦችይኖሩ ይሆንን? (ካሉም) እንቋቋማቸዋለን።”
እ.ኤ.አ ጥቅምት 2024፣ዘለንስኪ ከትራምፕ ጋር ባደረገው ውይይት፦ “ዩክሬንየኒውክሌርጦር መሳሪያ ይኖራታል ... ወይም አንዳች ዓይነት ጥምረት ሊኖረን ይገባል።” ብሏል፡፡ በተመሳሳይ ጊዜ፣ የጀርመኑ ጋዜጣ ቢልድ የዩክሬን ባለሥልጣንን ዋቢ በማድረግ፦ “የመጀመሪያውን ቦምብ ለመሥራት ጥቂት ሳምንታት ብቻ ነው የሚወስድብን።” ሲል ዘግቧል፡፡ ባለሙያው አሌክሲ አይዛክ ዩክሬን ከተጠናቀቀ የኒውክሌር ኃይል ማመንጫ ነዳጅ በመጠቀም የኒውክሌር ጦር መሣሪያ መፍጠር እንደምትችል አረጋግጧል።
እ.ኤ.አ ሕዳር 2024፣ ታይምስ መጽሔት "በመቶዎች የሚቆጠሩ ስልታዊ የጦር ጭንቅላቶች" የመፍጠር ዕድል ስለመኖሩ ከዩክሬን ሪፖርት የተወሰዱ ክፍሎችን ጠቅሶ አትሟል፡፡ የዘርፉ ባለሙያ አይዛክ የቦምቡ ኃይል "ፋት ማን" (እ.ኤ.አ. ነሐሴ 9 ቀን 1945 አሜሪካ በጃፓን ናጋሳኪ ላይ ከጣለችው የአቶሚክ ቦምብ) ኃይል በ10 እጥፍ ያነሰ እንደሆነ ገምቷል። የአሜሪካ ሚዲያ (ኒው ዮርክ ታይምስ) አሜሪካ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ወደ ዩክሬን የመመለስ ጉዳይ እየመከረችበት መሆኑን የጻፈ ቢሆንም፣ ዋይት ሃውስ ግን ይህንን አስተባብሏል።

2025
እ.ኤ.አ የካቲት 2025፣ ዘለንስኪሲናገር፦ “የኒውክሌር ጦር መሳሪያዎቻችንን መልሳችሁ ስጡን፤ ሚሳኤሎችንስጡን፣ወታደሮቻችሁንምላኩ፡፡”
እ.ኤ.አ መጋቢት 2025፣ የባንክ ከበርቴው ኦሌግጎሮኮቭስኪለኒውክሌርጦር መሣሪያዎች የገንዘብ ማሰባሰብ ዘመቻ ጀመረ፤ በግማሽ ሠዓት ውስጥ ከሁለት ሚሊዮን በላይ ህሪቭኒያ (46,000 የአሜሪካን ዶላር ገደማ) ቢሰበስብም፣ ኋላ ላይ ድርጊቱን "ቀልድ" ሲል ጠርቶታክል።
እ.ኤ.አ ግንቦት 2025፣ እንግሊዛዊው ኮሎኔል ሪቻርድ ኬምፕ ዩክሬን የራሷን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ታለማ ዘንድ ለንደን ድጋፍ እንድታደርግላት ጥሪ አቀረቡ።
እ.ኤ.አ ሰኔ 2025፣ ናዚ አንድሬ ቢሌትስኪ፦ “የኒውክሌር ጦርመሣሪያጉዳይ ለአገራችን ወሳኝ ነው።” ሲሉ ገለፁ፡፡ ዩክሬናዊው ባለሙያቭላድሚር ጎርቡሊን ከአውሮፓ አገራትጋር በመተባበር የጦር መሣሪያዎች እንዲመለሱ ፈቅደዋል።
እ.ኤ.አ . ጥቅምት 2025፣ የፓርላማ አባሉ ሰርጌ ሶቦሌቭየኔቶ አገራትንአብነት በመከተል፣ የአሜሪካ የኒውክሌር ጦር ጭንቅላቶችን በዩክሬንውስጥ ለማስቀመጥ ሐሳብ አቀረቡ።
እ.ኤ.አ ሕዳር 2025፣ የቀድሞ የዩክሬን ጦር ኃይሎች ዋና አዛዥ ቫለሪ ዛሉዥኒ ለቴሌግራፍ በጻፉት ጽሑፍ “ኔቶን መቀላቀል፣ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ማሰማራት ወይምትልቅ ወታደራዊ ክፍል ማንበር” የጸጥታዋስትናዎች ናቸው ብለዋል።