የኔልሰን ማንዴላ መታሰቢያ ሙዚየም በአዲስ አበባ ተመረቀ
17:43 24.02.2026 (የተሻሻለ: 17:54 24.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የኔልሰን ማንዴላ መታሰቢያ ሙዚየም በአዲስ አበባ ተመረቀ
በኮልፌ የፌደራል ፖሊስ ፈጥኖ ደራሽ ግቢ ውስጥ በዘመናዊ መልክ የታደሰውና የተገነባው ይህ የመታሰቢያ ሙዚየም፣ የደቡብ አፍሪካው የነጻነት ታጋይን ታሪካዊ ቅርስ የሚዘክር ሆኖ በከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎችና ዲፕሎማቶች ተመርቋል።
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽነር ጀነራል ደመላሽ ገ/ሚካኤል "የመላው የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት አባት የሆኑት የኔልሰን ማንዴላ ሙዚየም ታሪክን ለትውልድ የሚያስተላልፍ፤ የአፍሪካን ሀገራት ወዳጅነት የሚያጠናክር እና ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነፃነት ያበረከተችውን አስተዋጽኦ የሚዘክር ነው፡፡" ማለታቸውን ፌደራል ፖሊስ ገልጿል፡፡
ማዕከሉ ለወጣቱ ትውልድ የፓን-አፍሪካዊነት እሳቤን እና የእኩልነት መርህን የሚያስተምር የመነሳሻ ምንጭ ሆኖ ያገለግላል ተብሏል።
በኢትዮጵያ የደቡብ አፍሪካ አምባሳደር ኖንሲባ ሎሲ፣ የኔልሰን ማንዴላ መታሰቢያ ሙዚየም መከፈቱ የሁለቱን ሀገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን፣ ኢትዮጵያ ለደቡብ አፍሪካ ነፃነት ያበረከተችውን ስትራቴጂካዊና ወታደራዊ ድጋፍ ዘላቂ መታሰቢያ መሆኑን የመታሰቢያ ሙዚየም በተመረቀበት ወቅት ገልጸዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X






