ሱዳን ቴክኖሎጂን መሠረት አድርጎ ለሚገነባ 'ዘመናዊ ጦር' ቅድሚያ ትሰጣለች - አል-ቡርሃን
14:50 24.02.2026 (የተሻሻለ: 14:54 24.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ሱዳን ቴክኖሎጂን መሠረት አድርጎ ለሚገነባ 'ዘመናዊ ጦር' ቅድሚያ ትሰጣለች - አል-ቡርሃን
የጦር ኃይሉ አዛዡ በአቪዬሽን፣ በድሮን፣ በተንቀሳቃሽ የጦር መሣሪያዎች እና በመከላከያ ሥርዓቶች ላይ ምርምርን ለማሳደግ ስትራቴጂ መንደፋቸውን ተገልጿል፡፡ ወታደራዊ አቅምን ለማጠናከርም ወጣት መሐንዲሶችን እና ቴክኒሻኖችን በመመልመል ላይ መሆናቸውን የሽግግር ሉዓላዊ ምክር ቤት ገልጿል።
በካራሪ ዩኒቨርሲቲ ወታደራዊ የምረቃ ሥነ-ስርዓት ላይ ንግግር ያደረጉት አብደል ፋታህ አል-ቡርሃን፣ ዓመፁ እስኪያበቃ ድረስ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ሚሊሻን እንደሚዋጉ አጥብቀው ተናግረዋል።
በተጨማሪም በቅስቀሳ ወይም በተሳሳተ መረጃ ምክንያት መሣሪያ ላነሱ ተዋጊዎች የሰላም ጥሪ ያቀረቡ ሲሆን፣ ጠላትነታቸውን ለሚቀጥሉ ፖለቲከኞች ግን ተጠያቂነት እንደሚኖር አስጠንቅቀዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X