ኢትዮጵያዊቷ ሠዓሊ ሰላማዊት ገብረፃድቅ የሥዕል ሥራዎቿን በሞስኮ ለዕይታ አቀረበች
14:19 24.02.2026 (የተሻሻለ: 14:24 24.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያዊቷ ሠዓሊ ሰላማዊት ገብረፃድቅ የሥዕል ሥራዎቿን በሞስኮ ለዕይታ አቀረበች
ኢትዮጵያዊቷ አርቲስት ሰላማዊት ገብረፃድቅ ከዓለም ሕዝቦች ጉባኤ ድርጅት ጋር በመተባበር ያዘጋጀችው የሥነ-ጥበብ ዐውደ-ርዕይ በሩሲያ የሳይንስ አካዳሚ በደማቅ ሁኔታ ተከፍቶ ለዕይታ ቀርቧል።
ባሳለፍነው አርብ (የካቲት 13 ቀን 2018 ዓ.ም) የዐውደ-ርዕዩ መክፈቻ እና የአርቲስቷ የጥበብ አልበም ምርቃት፤ በሩሲያ የኢትዮጵያ ባለሙሉ ሥልጣን አምባሳደር ዶ/ር ገነት ተሾመ በተገኙበት በሞስኮ ተከናውኗል።
ሰዓሊ ሰላማዊት በዐውደ-ርዕዩ ላይ ለተገኙ ጎብኚዎች ስለ ሥራዎቿ ጥልቅ ማብራሪያ የሰጠች ሲሆን፣ ስራዎቿም በጎብኚዎች ዘንድ ከፍተኛ አድናቆትን አትርፈዋል።
የሰላማዊት የጥበብ አልበም በይፋ የማስመረቅ ሥነ-ስርዓት ነገ የካቲት 17 ቀን 2018 ዓ.ም በዓለም ሕዝቦች ጉባኤ አዳራሽ እንደሚካሄድ ይጠበቃል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X