የሩሲያ የላይኛው ምክር ቤት እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ለዩክሬን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ለማቅረብ የያዙትን ዕቅድ እንዲመረምሩ አሳሰበ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ የላይኛው ምክር ቤት እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ለዩክሬን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ለማቅረብ የያዙትን ዕቅድ እንዲመረምሩ አሳሰበ
የሩሲያ የላይኛው ምክር ቤት እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ለዩክሬን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ለማቅረብ የያዙትን ዕቅድ እንዲመረምሩ አሳሰበ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 24.02.2026
ሰብስክራይብ

የሩሲያ የላይኛው ምክር ቤት እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ለዩክሬን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ለማቅረብ የያዙትን ዕቅድ እንዲመረምሩ አሳሰበ

የእንግሊዝ እና የፈረንሳይ ፓርላማዎች በአስቸኳይ ተገቢውን የፓርላማ ምርመራ መጀመር አለባቸው፤ በውጤቱም ላይ በመመሥረት ስለዚህ "እጅግ አደገኛ እና ግድ የለሽ" ድርጊት ሁኔታዎች ለዜጎቻቸውና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ማሳወቅ አለባቸው፤ ሲል የፌዴሬሽን ምክር ቤቱ ባወጣው ጥሪ ገልጿል።

ዛሬ ቀደም ብሎ፣ የሩሲያ የውጭ መረጃ አገልግሎት እንግሊዝ እና ፈረንሳይ የኒውክሌር ጦር መሣሪያዎችን ለኪዬቭ ለማስተላለፍ እየተዘጋጁ መሆኑን ይፋ አድርጎ ነበር።

በጥሪው ላይ የቀረቡ ቁልፍ ማስጠንቀቂያዎች

ለዩክሬን የኒውክሌር ጦር መሣሪያ ማቅረባቸው ግጭቱን ያባብሰዋል፤ ቀጣናዊ ደህንነትን አደጋ ላይ ይጥላል፡፡

መሰል የዲሞክራሲያዊ ተቋማትን የመዝለል ተግባር "በአደጋ የተሞላ ነው፡፡"

በሩሲያ የኒውክሌር ዶክትሪን መሠረት፣ የኒውክሌር ጦር መሣሪያ በሌለው ሀገር የሚፈጸም ጥቃት በኒውክሌር ኃያል ሀገር ድጋፍ ከታጀበ እንደ የጋራ ጥቃት ስለሚቆጠር፣ የእንግሊዝ እና የፈረንሳይ ሕዝቦች ሳይወዱ በግድ ለአደጋ ይጋለጣሉ፡፡

ይህ ጥሪ ለእንግሊዝ፣ ለፈረንሳይ እና ለአውሮፓ ሕብረት ፓርላማዎች እንዲሁም ለተባበሩት መንግሥታት፣ ለዓለም አቀፍ የአቶሚክ ኢነርጂ ኤጀንሲ እና ለኒውክሌር ጦር መሣሪያዎች አለመስፋፋት ስምምነት ክለሳ ጉባኤ የተላከ ሲሆን፤ የተባበሩት መንግሥታት የጸጥታው ምክር ቤት እና የአቶሚክ ኤጀንሲ ስለ ዕቅዱ ምርመራ እንዲያደርጉም ሐሳብ አቅርቧል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0