ትራምፕ በኢራን ላይ የያዙት የወታደራዊ አማራጭ ውጤት ባለማምጣቱ መበሳጨታቸው ተዘገበ
10:41 24.02.2026 (የተሻሻለ: 10:44 24.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ትራምፕ በኢራን ላይ የያዙት የወታደራዊ አማራጭ ውጤት ባለማምጣቱ መበሳጨታቸው ተዘገበ
ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ እየተደረገ ያለው ወታደራዊ ጫና የሚፈለገውን ውጤት ባለማምጣቱ ብስጭት ውስጥ መሆናቸውን ሲቢኤስ ኒውስ ዘግቧል።
በቬንዙዌላ ከተካሄደው ዘመቻ በተለየ መልኩ፣ በቴህራን ላይ የሚሰነዘር ማንኛውም ጥቃት በመካከለኛው ምስራቅ ለረጅም ጊዜ የሚቆይ ግጭት የመቀስቀስ ስጋት አለው ተብሏል።
የጦር ኃይሎች ጠቅላይ ኢታማዦር ሹም ጄኔራል ዳን ኬይን በኢራን ላይ የሚደረግ ወታደራዊ ዘመቻ በአሜሪካ ኃይሎች ላይ የአጸፋ ጥቃት ሊያስከትል እንደሚችል አስጠንቅቀዋል።
ትራምፕ ግን ጄኔራል ኬይን ጦርነትን የሚቃወሙ ሳይሆኑ፣ በጦርነቱ "ማሸነፍ" ብቻ የሚፈልጉ መሆናቸውን አጥብቀው ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X