ቡርኪና ፋሶ በክትባት፣ በአጎበር እና በመከላከያ ህክምናዎች አማካኝነት በአንድ ዓመት ውስጥ የወባ በሽታን በ32 በመቶ መቀነሷን አስታወቀች
20:00 23.02.2026 (የተሻሻለ: 20:04 23.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቡርኪና ፋሶ በክትባት፣ በአጎበር እና በመከላከያ ህክምናዎች አማካኝነት በአንድ ዓመት ውስጥ የወባ በሽታን በ32 በመቶ መቀነሷን አስታወቀች
በሀገሪቱ ያለው አጠቃላይ የወባ ህመምተኞች ቁጥር እ.ኤ.አ. በ2024 ከነበረበት 10,805,020፣ በ2025 ወደ 7,329,278 ዝቅ ማለቱን የቡርኪና ፋሶ ጤና ሚኒስቴር በመግለጫው አስታውቋል። ይህም ከ2020 እስከ 2024 ይታይ የነበረውን የበሽታውን ስርጭት ሂደት በከፍተኛ ሁኔታ የቀለበሰ ስኬት ነው።
ለዚህ ለውጥ ምክንያት የሆኑት እርምጃዎች የሚከተሉት ናቸው፦
🟠 ካለፈው ዓመት ነሐሴ ጀምሮ በሁሉም 70 የጤና ወረዳዎች የተዘረጋው ነፃ የወባ ክትባት፣
🟠 ወደ 15 ሚሊዮን የሚጠጉ የዘመኑ ፀረ-ተባይ ማጥፊያ የተደረገባቸውን አጎበሮች በነፃ የማከፋፈል ሀገራዊ ዘመቻ፣
🟠 በበሽታው ስርጭት ወቅት ለ5 ወራት ያህል ከ5 ዓመት በታች ለሆኑ 4.9 ሚሊዮን ሕፃናት የሚሰጥ የወባ መከላከያ መድኃኒት፣
🟠 ለነፍሰ ጡር ሴቶች የሚሰጥ የበሽታው ቅደሚያ መከላከያ ሕክምና እንዲሁም
🟠 በሽታውን ቀድሞ የመለየት እና የታመሙ ሰዎችን የመንከባከብ ስራን ማጠናከር።
በጎርጎሮሳዊያኑ 2030 ወባን ከቡርኪና ፋሶ ሙሉ በሙሉ ማጥፋት የሀገሪቱ መንግሥት ዋነኛ ግብ ሆኗል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X