አሜሪካ 16 የጦር መርከቦችን እና 40 ሺህ ወታደሮችን በመካከለኛው ምስራቅ እያሰባሰበች መሆኑ ተዘገበ
10:49 23.02.2026 (የተሻሻለ: 10:54 23.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
አሜሪካ 16 የጦር መርከቦችን እና 40 ሺህ ወታደሮችን በመካከለኛው ምስራቅ እያሰባሰበች መሆኑ ተዘገበ
በተጨማሪም፣ አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ በሚገኙ ወታደራዊ ካምፖቿ ውስጥ አምስት የጥቃት የአየር ክንፎች (ከብርጌድ የሚመጣጠን መዋቅር)፣ 70 ገደማ አውሮፕላኖችን የሚይዙ የዕዝ ክፍሎች የነበሯት ሲሆን፣ አሁን ደግሞ በዩኤስ አብርሃም ሊንከን እና በዩኤስኤስ ጄራልድ አር ፎርድ የአውሮፕላን ተሸካሚ መርከቦች ላይ ተጨማሪ ሁለት የአየር ክንፎችን መጨመሯን የአሜሪካ መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
ቀደም ሲል፣ ትራምፕ "ግዙፍ የባሕር ኃይል ጦር" ወደ ኢራን አቅጣጫ እየተጓዘ መሆኑን በመግለጽ፣ የኒውክሌር መሣሪያዎችን ለማስወገድ የሚያስችል ስምምነት እንዲደረግ አሳስበዋል።
የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ በበኩላቸው፣ በጥር ወር መጨረሻ ላይ በሰጡት መግለጫ፣ ቴሕራን ዩራኒየምን የማበልጸግ መብቷን እንደማትተው፣ ይህም "ወደ ጦርነት ቢመራም እንኳ" አቋሟን እንደማትቀይር አጥብቀው ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X