“የገጸ ምድርና የከርሰ ምድር ውሃ ሃብቶች ለመስኖ ልማት በመዋላቸው በሀገሪቱ የግብርና ዘርፍ ከፍተኛ ለውጥ እየተመዘገበ ነው" - ዐቢይ አሕመድ

ሰብስክራይብ

“የገጸ ምድርና የከርሰ ምድር ውሃ ሃብቶች ለመስኖ ልማት በመዋላቸው በሀገሪቱ የግብርና ዘርፍ ከፍተኛ ለውጥ እየተመዘገበ ነው" - ዐቢይ አሕመድ

የብላቴ በረሃ የሰው ልጅ በርትቶ ከሠራ ምን ሊያመጣ እንደሚችል የሚያመላክት መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ በካባቢው ባደረጉት ጉብኝት ወቅት ተናግረዋል፡፡

“ከዚህ ቀደም ጥቅም ሳይሰጡ የቆዩ በርካታ ቦታዎች አሁን ላይ በመስኖ ወደ ግብርና ልማት ማዕከልነት እየተቀየሩ ነው። የብላቴ ወንዝ የሚገኝበት አካባቢ ደግሞ ለዚህ ተጠቃሽ አብነት ነው። በአካባቢው የግል ባለሃብቶችን በማሳተፍ ሰፋፊ የፍራፍሬ ልማቶች እየተከናወኑ ይገኛል። ይህም የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥ የሚደረገውን ጥረት በእጅጉ የሚያግዝ ነው።”

የኢትዮጵያው መሪ፣ በብላቴ ወንዝ አካባቢ የተከናወነ ስለሚገኘው ሰፊ የግብርና ሥራ አስመልክቶ ያደረጉትን ንግግር በቪዲዮው ይመልከቱ ፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0