ብሪክስ ለኢ-ፍትሐዊ የዓለም ሥርዓት አስፈላጊ አማራጭ ነው - ፕሮፌሰር

ሰብስክራይብ

ብሪክስ ለኢ-ፍትሐዊ የዓለም ሥርዓት አስፈላጊ አማራጭ ነው - ፕሮፌሰር

​በደቡብ አፍሪካ የኬፕ ታውን ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ጥናት ክፍል ኃላፊ ዝዌሌቱ ጆሎቤ ለስፑትኒክ አፍሪካ እንደተናገሩት፣ በደቡባዊው የዓለም ክፍል የሚገኙ በርካታ አገራት "ባለብዙ-ዋልታ" የዓለም ሥርዓትን ፍትሐዊ አሰራርን ለመገንባት እንደ ትልቅ ዕድል ይመለከቱታል።

በዚህም መሠረት ብሪክስ የአፍሪካን ዓለም አቀፋዊ ቦታ እንደገና ለመደራደር እንደ ዋነኛ መሣሪያ እየታየ መሆኑን ገልጸዋል።

​ እንደ ጆሎቤ ገለጻ፣ በአሜሪካ ውስጥ የሚካሄዱ ክርክሮች፣ የበላይነትን በባለብዙ ወገን ተቋማት ወይንም በቀጥታ የኃይል እርምጃ ስለማስቀጠል የሚመከሩት አሁንም ትኩረታቸው የአሜሪካን የበላይነት በዶላር አማካኝነት ጭምር ለማስጠበቅ ነው። ይህ ሁኔታ ደግሞ በርካታ አገራት አማራጮችን እንዲፈልጉ አነሳስቷቸዋል ሲሉ ሞግተዋል።

ከሶቪዬት ሕብረት ጋር ጥልቅ የታሪክ ትስስር ባላቸው የደቡባዊ አፍሪካ አገራት ዘንድ፣ ብሪክስ ከስትራቴጂካዊ ጥምረት በላይ እንደ እኩልነት ማዕቀፍ ይታያል ሲሉ ጆሎቤ ጠቅሰዋል።

በርካታ የአፍሪካ አገራት ብሪክስን፣ አባላት በእኩልነት የሚሳተፉበት፣ በጠበበ የግል ፍላጎት ላይ ሳይሆን በጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ የንግድ፣ የልማት እና የትብብር መድረክ አድርገው እንደሚመለከቱት አጽንኦት ሰጥተዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0