ኒጀር የሳሕል አገራት ጥምረት የሁለተኛ ዓመት ፍኖተ-ካርታን አጸደቀች
18:38 22.02.2026 (የተሻሻለ: 18:44 22.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኒጀር የሳሕል አገራት ጥምረት የሁለተኛ ዓመት ፍኖተ-ካርታን አጸደቀች
የመከላከያ እና ደህንነት፣ ዲፕሎማሲ እንዲሁም ልማት የተባሉትን ሦስት ዋና ዋና ምሰሶዎች ያካተተው ረቂቅ ሰነድ፣ በኒያሜ በተካሄደው የሳሕል አገራት ጥምረት ብሔራዊ ኮሚቴ ስብሰባ መፅደቁን ጠቅላይ ሚኒስትር አሊ ማሃማን ዜይን አስታውቀዋል።
ዜይን ሲናገሩም፣ "አስፈላጊውን መመሪያ ሰጥተናል፤ የተወሰኑ የውሳኔ ሃሳቦችን አጽድቀናል፣ እርማቶችን አድርገናል፤ እንዲሁም አስፈላጊ በሆኑ ቦታዎች ላይ እንደገና እንዲቀረጹ ጨምሮ ተጨማሪ አስተያየቶችን አቅርበናል" ብለዋል።
ረቂቁ የተላለፈው የዘንድሮውን የሳሕል ጥምረት አገራት ተዘዋዋሪ ሊቀመንበርነት በያዘችው ቡርኪና ፋሶ በኩል ነው።
ከየካቲት 17 እስከ 19 የሳሕል አገራት ጥምረት ከፍተኛ ባለስልጣናት እና ሚኒስትሮች የማሊን የውሳኔ ሃሳቦች ለመመርመር በቡርኪና ፋሶ ይሰበሰባሉ፡፡ ከዚያም የተጠናከረ ፍኖተ-ካርታ ለመጨረሻ ጊዜ እንዲፀድቅ ለሀገራቱ መሪዎች ምክር ቤት ይቀርባል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X