"ኤሊት ፎርስ የምንገነባው በቀጣናችን ውጊያ እና ሽብር እንዳይፈጠር፤ ሲፈጠርም በአጭር ጊዜ ለመቋጨት ነው" – ዐቢይ አሕመድ

ሰብስክራይብ

"ኤሊት ፎርስ የምንገነባው በቀጣናችን ውጊያ እና ሽብር እንዳይፈጠር፤ ሲፈጠርም በአጭር ጊዜ ለመቋጨት ነው" – ዐቢይ አሕመድ

“የኛ ዝግጅት ለአፍሪካ ሰላምና ብልጽግና ለማረጋገጥ በቀጣናችን ላሉት ሀገራት አለኝታ፣ ጋሻ እና መከታ ለመሆን ነው” ሲሉ የጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በሐዋሳ ስቴዲየም በተከበረው የልዩ ዘመቻዎች ዕዝ 65ኛ ዓመት የምሥረታ በዓል ላይ ባደረጉት ንግግር ገልፀዋል፡፡

ኢትዮጵያ ከሶማሌ ጫፍ እስከ ምፅዋ ጫፍ በባሕር የሚያጋጥሙ ሽብሮችን ለማስቀረት፣ ልማት እና ብልጽግናን ለማረጋገጥ ወንድም ሕዝቦችን በመደገፍ ትሠራለች ብለዋል፡፡

"ቴኖሎጂን የታጠቀ፣ ቴክኖሎጂን የሚጠቀም፣ በድሮን ረኮንሰንስ የሚያደግ በካሚካዚ ምሽግ የሚያፈርስ፣ በምሽግ ብቻ ሳይሆን በስትራቴጂክ ቦታዎች፣ በሰላም ወረዳዎች ውጊያን የሚያጧጡፍና የሚያሳጥር ተቋም ኢትዮጵያ ስለገነባች ድፍን አፍሪካ ድፍን የምስራቅ አፍሪካ ሀገራት እንኳን ደስ አላችሁ፤ እንኳን ደስ አለን፡፡” በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0