ቡርኪና ፋሶ እና ጋና የደህንነት እና የንግድ ትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
10:45 22.02.2026 (የተሻሻለ: 10:54 22.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ቡርኪና ፋሶ እና ጋና የደህንነት እና የንግድ ትብብር ስምምነት ተፈራረሙ
ስምምነቶቹ የተፈረሙት በቡርኪና ፋሶው ጠቅላይ ሚኒስትር ሪምታልባ ዣን ኢማኑኤል ኦኤድራጎ እና በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሙኤል ኦኩዜቶ አብላክዋ በሚመራው የጋና ልዑካን ቡድን መካከል የተደረገውን ውይይት ተከትሎ መሆኑን የቡሪኪና ፋሶ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ቁልፍ ስምምነቶችም፦
የሸቀጦች እና የሰዎች እንቅስቃሴን ለማሳለጥ የብሔራዊ የመንጃ ፈቃዶች የጋራ እውቅና፣
ድንበር ተሻጋሪ የትብብር ማዕቀፍ፣
የጋራ የአደጋ ጊዜ አስተዳደር ዘዴዎች፣
የአደንዛዥ ዕፅ ዝውውርን በመዋጋት ላይ መተባበር እና
የመረጃ መጋራት፣ ሥልጠና እና ሽብርተኝነትን መከላከልን ጨምሮ የደህንነት ትብብርን ማሳደግ ያካትታል፡፡
ሁለቱ አገራት ቁርጠኝነታቸውን ወደ ተጨባጭ ተግባር በመቀየር በታሪክ፣ በመልካምድር እና በጋራ ቁርጠኝነት የወደፊት የሰላም፣ የጸጥታ እና የጋራ ብልጽግናን ለመገንባት ዜጎቻቸውን የሚጠቅሙ ተግባራትን ለማከናወን ማቀዳቸውን ጽሕፈት ቤቱ ገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X