ሩሲያ ከተሳተፈች ኡጋንዳ በእጅጉ ትጠቀማለች - ተንታኝ
19:49 21.02.2026 (የተሻሻለ: 19:54 21.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ሩሲያ ከተሳተፈች ኡጋንዳ በእጅጉ ትጠቀማለች - ተንታኝ
በሩሲያ የሚደገፍ የፀሐይ ኃይል ማምረቻ የኡጋንዳን የግብርና ምርታማነት ያሳድጋል፤ ይህም ቀድሞውኑ 70 በመቶ የሚሆኑ ኡጋንዳውያንን ወደ ገንዘብ ኢኮኖሚ ውስጥ ያስገባውን 'ፐርሽ' (የኡጋንዳ አነስተኛ የአስተዳደር ክልል) ልማት ሞዴል ያጠናክረዋል፤ ሲሉ የካምፓላ ጋዜጠኛ እና የቀጣናው የፖለቲካ ተንታኝ ቶማስ ኤርነስት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡
ኤርነስት በነዳጅ እና ጋዝ ዘርፍ ያለውን ትብብርም ጠቁመው፣ የላቀ ቴክኖሎጂ ማግኘት፣ የባለሙያዎች ሥልጠና እና የእሴት ጭማሪ የሀገሪቱን ኢኮኖሚያዊ ዕድገት እንደሚያፋጥኑ ገልጸዋል።
የሩሲያ ወታደራዊ ድጋፍ፣ የከፍተኛ ቴክኖሎጂ መሣሪያዎችን እና መሰረተ ልማቶችን ጨምሮ፣ የኡጋንዳን ሉዓላዊነት የበለጠ እንደሚያስጠብቅም ተንታኙ ጠቅሰዋል።
የሩሲያ ድጋፍ ቴክኖሎጂን፣ የኒውክሌር ኃይልን፣ ግብርናን፣ መሠረተ ልማትን፣ ደህንነትን፣ ትምህርትን እና ኢንቨስትመንትን ያጠቃልላል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ ይህም ለሀገሪቱ ሰፊና ዘላቂ ጥቅሞችን እንደሚያስገኝ ተገልጿል።
ባለብዙ-ዋልታ ዓለም ለምን ሚዛናዊነትን፣ ብዝኃነትን እና አዳዲስ የዓለም አቀፍ የኃይል ማዕከላትን እንደሚያመጣ ለማወቅ የኤርነስትን ንግግር ያዳምጡ።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X