የአባት ሀገር ጠባቂዎች ቀን፦ ዚምባብዌ ከሩሲያ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ የመከላከያ ግንኙነት አደሰች

ሰብስክራይብ

የአባት ሀገር ጠባቂዎች ቀን፦ ዚምባብዌ ከሩሲያ ጋር ያላትን ስትራቴጂካዊ የመከላከያ ግንኙነት አደሰች

​ የሁለቱ አገራት ግንኙነት ዚምባብዌ ለነፃነት በምታደርገው ተጋድሎ ወቅት ሞስኮ ለሃራሬ ካሳየችው አጋርነትና ድጋፍ ጀምሮ የቆየ መሆኑን የመከላከያ ሚኒስትሯ ኦፓ ሙቺንጉሪ-ካሺሪ በዛሬው ዕለት ገልጸዋል።

​ሉዓላዊ አገራት ያለምንም ጫና ወይም ማዕቀብ የራሳቸውን የልማት ጎዳና እንዲወስኑ መፈቀድ እንዳለበት የገለጹት ሙቺንጉሪ-ካሺሪ፣ የባለብዙ ወገን የዓለም ሥርዓት አስፈላጊነትንም አፅንዖት ሰጥተውበታል።

ሚኒስትሯ፣ ሃራሬ የጋራ መከባበርንና በሌሎች አገራት የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ አለመግባትን የሚያበረታቱ የሁለትዮሽ እና የባለብዙ ወገን አጋርነቶችን ለማጠናከር ያላትን ቁርጠኝነት በድጋሚ አረጋግጠዋል። ሁለቱም ወገኖች ግንኙነታቸውን "በጊዜ የተፈተነ ወዳጅነት" ሲሉ የሚገልጹት ሲሆን፣ ግንኙነቱም በመከላከያ ስምምነቶችና በጋራ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴዎች እየጠነከረ መጥቷል።

​ በየዓመቱ የካቲት 14፣ የሚከበረው የ"አባት ሀገር ጠባቂዎች ቀን" የሩሲያን የጦር ኃይሎች አባላትን የሚያከብርና የአገሪቱን ወታደራዊ ቅርስ የሚዘክር በዓል ነው።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0