መልቲ-ቾይስ የኢትዮጵያን ተማሪዎች በዲጂታል ክህሎት ለማብቃት አዲስ መርሃ-ግብር ይፋ አደረገ
15:54 21.02.2026 (የተሻሻለ: 16:04 21.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
መልቲ-ቾይስ የኢትዮጵያን ተማሪዎች በዲጂታል ክህሎት ለማብቃት አዲስ መርሃ-ግብር ይፋ አደረገ
‘የኢትዮጵያ የወደፊት ክህሎቶች’ የተሰኘው መርሃ-ግብር በአዲስ አበባ ከሚገኙ የመንግስት ትምህርት ቤቶች የተመረጡ ተስፋ ሰጪ ተማሪዎችን በመሰረታዊ የዲጂታል እና የኮዲንግ ክህሎቶች ለማብቃት ያለመ መሆኑን ድርጅቱ አስታውቋል።
በመርሃ - ግብሩ፦
30 ያህል ከፍተኛ ብቃት ያላቸውን ተማሪዎች ለ12 ሳምንታት ለሚቆይ ሥልጠና ይቀበላል።
50 በመቶ የመርሃ ግብሩ ተሳታፊዎች ሴት ተማሪዎች ይሆናሉ።
ተማሪዎቹ ሳይንስ፣ ቴክኖሎጂ፣ ኢንጂነሪንግ እና ሂሳብ፣ ኮዲንግ፣ ፕሮግራሚንግ እንዲሁም እንደ የቡድን ሥራ እና ችግር መፍታት ያሉ ‘ለስላሳ ክህሎቶችን’ እንደሚማሩ ገልጿል።
ሥልጠናው በሥነ-አመክንዮአዊ አስተሳሰብ፣ በድረ-ገጽ መሠረቶች እና በሰው ሠራሽ አስተውሎት የታገዘ የላቀ ትምህርት ላይ ያተኩራል ሲሉ የሀገር ውስጥ መገናኛ ብዙሃን ዘግበዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X