'የኢትዮጵያ ታምርት' ሩጫን ዓለማቀፋዊ ይዘት የሚያሰጥ የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ

ሰብስክራይብ

'የኢትዮጵያ ታምርት' ሩጫን ዓለማቀፋዊ ይዘት የሚያሰጥ የመግባቢያ ስምምነት ተፈረመ

የጋራ መግባቢያ ስምምነቱን የኢንዱስትሪ ሚኒስቴርን በመወከል'የኢትዮጵያ ታምርት' ሩጫ አስተባባሪ አብዱልፈታ የሱፍ እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዘዳንት አትሌት ስልሽ ስህን ተፈራርመዋል።

የስምምነቱ ዓላማ የኢትዮጵያ ታምርት ሩጫን ዓለማቀፋዊ ደረጃን (ስታንዳርድ) ያሟላ በማድረግ ለአትሌቶች የስኬት አንዱ መንገድ እንዲሆን ለማስቻልና የሌሎች ዓለም ሀገራት ታዋቂና አዳዲስ አትሌቶችን ያካተተ ሆኖ እንዲቀጥል ጉልህ ሚና እንዲኖረው ማስቻል ነው፡፡

4ኛው የኢትዮጵያ ታምርት ሩጫ  ኢትዮጵያ ታምርት ለሁለንተናዊ ሉዓላዊነት በሚል መሪ ቃል በመጪው ሚያዚያ 18  ይካሄዳል ሲል ሚኒስቴሩ አስታውቋል።

ቪዲዮ፡- ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም የተካሄደው የኢትዮጵያ ታምርት ሩጫ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0