ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ የዲጂታል ስትሪሚንግ አገልግሎት አስጀመረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱኢትዮ ቴሌኮም አዲስ የዲጂታል ስትሪሚንግ አገልግሎት አስጀመረ
ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ የዲጂታል ስትሪሚንግ አገልግሎት አስጀመረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 20.02.2026
ሰብስክራይብ

ኢትዮ ቴሌኮም አዲስ የዲጂታል ስትሪሚንግ አገልግሎት አስጀመረ

አገልግሎቱ ይዘት ፈጣሪዎች፣ ፕሬዲዩሰሮች፣ የቴሌቪዥን ጣቢያዎች እንዲሁም መንግሥታዊና መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትና ግለሰቦች ጭምር የፈጠራ ሥራዎቻቸውን በቴሌ ብር ተደራሽ የሚያደርጉበት አዲስ ዲጂታል አማራጭ ነው ተብሏል።

ከመዝናኛና የፈጠራ ሥራዎች ባለፈ ትምህርት ነክ ይዘቶች በመላ ሀገሪቱ 24/7 ተደራሽ የሚሆኑበት 'ናሽናል ዲጂታል ኮንቴንት ፕላትፎርም' እንደሆነም የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ሥራ አስፈጻሚ ፍሬህይወት ታምሩ ገልጸዋል።

“ፕሮዲዩሰሮች፣ ሚዲያዎች፣ ይዘት ፈጣሪዎች ሥራዎቻቸውን ይዘው ይመጣሉ እኛም በቴሌብር አገልግሎት ለተጠቃሚዎች እናደርሳለን፤ ክፍያውም በቴሌ ብር ይፈጸማል” ብለዋል።

ለስርጭት አገልግሎቱ የሚሆኑ 10 ሺህ ገደማ በሲም ካርድ የሚሠሩ አነስተኛ ማሠራጫ ዲኮደሮች በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያ መቅረባቸውንም አስታውቀዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0