ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ በግማሽ ዓመቱ ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷ ተገለፀ
19:36 20.02.2026 (የተሻሻለ: 19:44 20.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ ከቱሪዝም ዘርፍ በግማሽ ዓመቱ ከ2.6 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ማግኘቷ ተገለፀ
ይህ ገቢ ሀገሪቱ ባለፉት ስድስት ወራት ውስጥ ካስተናገዳቻቸው ከ700 ሺህ በላይ ዓለም አቀፍ ጎብኚዎች መገኘቱን የቱሪዝም ሚኒስቴር አስታውቋል፡፡
የቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ እንደገና አበበ ከብሔራዊ ቴሌቪዥን ጋር በነበራቸው ቆይታ ለዘርፉ ዕድገት ቁልፍ ያሏቸውን ምክንያቶች ጠቅሰዋል፦
ታላላቅ ዓለም አቀፍ ጉባኤዎች በአዲስ አበባ መካሄዳቸው፣
“ኢትዮጵያን ይጎብኙ” (Visit Ethiopia) ዲጂታል ድረ-ገጽ፣
የአዳዲስ መዳረሻዎች መገንባትና የነባሮች ዕድሳት፡፡
የተባበሩት መንግሥታት የቱሪዝም ድርጅት፤ ኢትዮጵያን በዘርፉ ፈጣን ዕድገት እያሳዩ ካሉ የቱሪዝም መዳረሻ ሀገራት ዝርዝር ውስጥ ማካተቱ ይታወሳል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X


