በወላይታ ዞን 81 ሚሊዮን ቶን የድንጋይ ከሰል ክምችት መኖሩ ተረጋገጠ
15:33 20.02.2026 (የተሻሻለ: 15:44 20.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በወላይታ ዞን 81 ሚሊዮን ቶን የድንጋይ ከሰል ክምችት መኖሩ ተረጋገጠ
ይህ የማዕድን ክምችት መጠን በወላይታ ዞን ኪንዶ ዲዳዬ ወረዳ በ81 ካሬ ኪሎ ሜትር ክልል ውስጥ እንደሚገኝ ባካሄደው ጥናትና ምርምር ማረጋገጡን የኢትዮጵያ ጂኦሎጂካል ኢንስቲትዩት አስታውቋል።
የተገኘው የድንጋይ ከሰል፤ ለሲሚንቶ ማምረቻ፣ ለኢንዱስትሪ ቦይለሮች እና ለጡብ ፋብሪካዎች እንደ ዋነኛ የኃይል ምንጭነት ማገልገል እንደሚችል ተጠቁሟል።
በደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት በኦሞ ተፋሰስ የተገኘው ይህ የድንጋይ ከሰል ክምችት ለኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ዘርፍ መስፋፋት ወሳኝ ሚና ይጫወታል ተብሏል።
ኢትዮጵያ ለድንጋይ ከሰል ግዢ በየዓመቱ ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ የውጭ ምንዛሬ እንደምታወጣ የማዕድን ሚኒስቴር መግለፁ ይታወሳል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X