የሊቢያ የፖለቲካ አንድነት ለሀገሪቱ ሰላም ቁልፍ መሆኑን የሩሲያ መልዕክተኛ ገለፁ
20:03 19.02.2026 (የተሻሻለ: 20:04 19.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሊቢያ የፖለቲካ አንድነት ለሀገሪቱ ሰላም ቁልፍ መሆኑን የሩሲያ መልዕክተኛ ገለፁ
በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የሩሲያ መልዕክተኛ ቫሲሊ ኔቤንዚያ፤ አንድነቱ በሁሉም የሊቢያ መስኮች መደበኛ ሕይወት ለመመለስ መሠረታዊ ነው ሲሉ በጸጥታው ምክር ቤት ስብሰባ ላይ ተናግረዋል።
"በሊቢያ የሰላም ሂደት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅትን የአስተባባሪነት ሚና እንገነዘባለን" ብለዋል።
የሩሲያ ቋሚ ተወካይ ዋና ዋና ነጥቦች፦
🟠 ሩሲያ፤ በሊቢያ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ዋና ጸሐፊ ልዩ ተወካይ እና የድጋፍ ተልዕኮ ኃላፊ ሃና ቴቴ፤ ሀገር አቀፍ ምርጫ ለማካሄድ እንቅፋት የሆኑ ጉዳዮችን ለማስወገድ የሚያደርጉትን ጥረት ጨምሮ ሌሎች የተመድ ተነሳሽነቶችን ትደግፋለች።
🟠 በሊቢያ የፖለቲካ አንድነት ለማምጣት የሚከናወነው ሥራ ወጥ እና በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሠረት መከናወን አለበት።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X