የጋና የባሪያ ንግድ የውሳኔ ሃሳብ በጉዳዩ ዙሪያ የሚደረገውን ውይይት ከዝክር ወደ ፍትሕ ሊቀይር ይችላል - ተሟጋች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየጋና የባሪያ ንግድ የውሳኔ ሃሳብ በጉዳዩ ዙሪያ የሚደረገውን ውይይት ከዝክር ወደ ፍትሕ ሊቀይር ይችላል - ተሟጋች
የጋና የባሪያ ንግድ የውሳኔ ሃሳብ በጉዳዩ ዙሪያ የሚደረገውን ውይይት ከዝክር ወደ ፍትሕ ሊቀይር ይችላል - ተሟጋች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.02.2026
ሰብስክራይብ

የጋና የባሪያ ንግድ የውሳኔ ሃሳብ በጉዳዩ ዙሪያ የሚደረገውን ውይይት ከዝክር ወደ ፍትሕ ሊቀይር ይችላል - ተሟጋች

ጋና የአትላንቲክ የባሪያ ንግድን በሰው ልጆች ላይ የተፈጸመ ከባድ ወንጀል ብሎ በመፈርጅ፤ "በከፍተኛ የዲፕሎማሲ ደረጃ የዓለምን ታሪካዊ መዝገብ ለማረም" ያለመ

የውሳኔ ሃሳብ ለተመድ አቅርባለች ሲሉ የጋና ፓን-አፍሪካን ፕሮግረሲቭ ፍሮንት የቅንጅት ኮሚቴ አባል እና የዋና መሥሪያ ቤት ኃላፊ ሀምፍሪ አቢ ኩዋዬ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።

የኩዋዬ ቁልፍ ምልከታዎች፦

🟠 በአፍሪካ ኅብረት በኩል የሚደረግ ቀጣናዊ ድጋፍ "የአኅጉሪቱን አንድነት የሚያሳይ እና የአፍሪካን የጋራ ድምጽ የሚያጠናክር" ይሆናል።

🟠 የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት በይፋ በወንጀልነት ካወገዘው፤ "ካሳ የፍትሕ እንጂ የልግስና ጉዳይ አይደለም" የሚለውን መከራከሪያ ያጠናክራል።

🟠 የውሳኔ ሃሳቡ አሁን ያለው ኢኮኖሚያዊ አለመመጣጠን "በታሪክ የተፈጠረ" እና መሠረቱ የቅኝ አገዛዝ ብዝበዛ መሆኑን ያጎላል።

ኩዋዬ፤ እንቅስቃሴውን ለማስቀጠል የሚከተሉት ነጥቦች አስፈላጊ እንደሆኑ አጽንኦት ሰጥተዋል፦

🟠 ከካሪቢያን እና ከደቡባዊው ዓለም አጋሮች ጋር ትብብር ማጠናከር።

🟠 ጉዳዩን በተባበሩት መንግሥታት ግምገማዎች እና በመዋቅራዊ ውይይቶች ማስቀጠል።

🟠 "ይህ የአንድ ጊዜ የዲፕሎማሲ ጉዳይ ብቻ መሆን የለበትም። ወደተደራጁ ድርድሮች፣ የፖሊሲ ሀሳቦች እና ሊለኩ ወደሚችሉ ማዕቀፎች ማደግ አለበት" ብለዋል።

"ካሳ ቅጣት ሳይሆን ማገገሚያ ነው። የአትላንቲክ የባሪያ ንግድ እና ቅኝ አገዛዝ ለምዕራባውያን ትውልዳዊ ሀብት፤ በአፍሪካ ደግሞ ትውልዳዊ ድህነት አስከትለዋል" ሲሉ ኩዋዬ አብራርተዋል።



በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0