የቤላሩስ ፕሬዚዳንት ከሞዛምቢክ እና ዚምባብዌ ጋር የባሕር ወደብ ግንባታ የሦስትዮሽ ፕሮጀክት ሃሳብ አቀረቡ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየቤላሩስ ፕሬዚዳንት ከሞዛምቢክ እና ዚምባብዌ ጋር የባሕር ወደብ ግንባታ የሦስትዮሽ ፕሮጀክት ሃሳብ አቀረቡ
የቤላሩስ ፕሬዚዳንት ከሞዛምቢክ እና ዚምባብዌ ጋር የባሕር ወደብ ግንባታ የሦስትዮሽ ፕሮጀክት ሃሳብ አቀረቡ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.02.2026
ሰብስክራይብ

የቤላሩስ ፕሬዚዳንት ከሞዛምቢክ እና ዚምባብዌ ጋር የባሕር ወደብ ግንባታ የሦስትዮሽ ፕሮጀክት ሃሳብ አቀረቡ

በቤላሩስ ጉብኝት እያደረጉ ከሚገኙት የዚምባብዌ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ሜብል ሜሞሪ ቺኖሞና ጋር የተወያዩት አሌክሳንደር ሉካሼንኮ፤ “በአፍሪካ አኅጉር ደቡብ ምስራቅ የባሕር ዳርቻ ላይ ጠንካራ ይዞታ ያስፈልገናል” ብለዋል።

ሉካሼንኮ ከሞዛምቢክ እና ዚምባብዌ ጋር በመተባበር የባቡር አገልግሎትን ወደ ነበረበት በመመለስ፤ ሀገሪቱን በተለይም ከሩሲያ እና ከቤላሩስ ለሚመጡ ሸቀጦች ቁልፍ ማዕከል ማድረግ እንደሚቻል ጠቁመዋል ሲል የፕሬዚዳንቱ የፕሬስ አገልግሎት ገልጿል።

ሉካሼንኮ፤ ቤላሩስ እና ዚምባብዌ የ100 ሚሊዮን ዶላር የንግድ ልውውጥ ግብ ለማሳካት የተቀመጠውን ፍኖተ-ካርታ መከተል እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተዋል። ለስምምነቶቹ ትግበራም የሁለቱ ሀገራት ፓርላማዎች የክትትል ሚና ከፍተኛ እንደሆነ አክለዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0