ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ በ "ስቴብል ኮይን" ፍላጎት ዕድገት ቀዳሚ ሆኑ - ጥናት
16:34 19.02.2026 (የተሻሻለ: 16:44 19.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ናይጄሪያ እና ደቡብ አፍሪካ በ "ስቴብል ኮይን" ፍላጎት ዕድገት ቀዳሚ ሆኑ - ጥናት
"የስቴብል ኮይን አገልግሎት ሪፖርት" በሚል ርዕስ ዩጎቭ ከክሪፕቶ ኩባንያዎቹ ቢቪኤንኬ፣ ኮይንቤዝ እና አርቴሚስ ጋር በመተባበር ባደረገው ጥናት መሠረት፤ 80 በመቶ የሚጠጉ የናይጄሪያ እና የደቡብ አፍሪካ ምላሽ ሰጪዎች "ስቴብል ኮይን" አላቸው። ከነዚህም ውስጥ ከ75 በመቶ በላይ የሚሆኑት በሚቀጥለው ዓመት የክሪፕቶ ይዞታቸውን ለማሳደግ አቅደዋል።
ስቴብል ኮይንን የመግዛት ፍላጎት ዝቅተኛ እና መካከለኛ ገቢ ባላቸው ሀገራት ውስጥ ከፍተኛ ነው። ይህም ከፍተኛ ገቢ ካላቸው ሀገራት ጋር ሲነፃፀር በእጥፍ ይበልጣል።
በተለይም 95 በመቶ የሚሆኑ ናይጄሪያውያን ከሀገሪቱ ገንዘብ "ናይራ" ይልቅ ክፍያዎችን በ "ስቴብል ኮይን" መቀበል ይመርጣሉ።
የደቡብ አፍሪካ ማዕከላዊ ባንክ ገዢ ሌሴትጃ ካጋንያጎ፤ ስቴብል ኮይን ከፍተኛ የሃዋላ ክፍያን እንደሚቀንስ በመግለፅ
ስለጠቀሜታው አብራርተዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X