ፌስታል ላይ የተጣለውን እገዳ ተከትሎ ተኪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያው ለማቅረብ ከሕንድና ቻይና ኩባንያዎች ጋር ውይይት ተጀመረ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱፌስታል ላይ የተጣለውን እገዳ ተከትሎ ተኪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያው ለማቅረብ ከሕንድና ቻይና ኩባንያዎች ጋር ውይይት ተጀመረ
ፌስታል ላይ የተጣለውን እገዳ ተከትሎ ተኪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያው ለማቅረብ ከሕንድና ቻይና ኩባንያዎች ጋር ውይይት ተጀመረ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 19.02.2026
ሰብስክራይብ

ፌስታል ላይ የተጣለውን እገዳ ተከትሎ ተኪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያው ለማቅረብ ከሕንድና ቻይና ኩባንያዎች ጋር ውይይት ተጀመረ

ይህም በአዲስ አበባ ከተማ በተተኪ የፌስታል ምርት ግብዓቶች ላይ የታየውን ከፍተኛ የዋጋ ንረት ተከትሎ የመጣ ነው።

ችግሩን ለመቅረፍ ከውጭ አምራች ኩባንያዎች ጋር ንግግር ላይ መሆኑን የከተማዋ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል።

የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ “በአሁኑ ወቅት በገበያ ላይ ያለው የተተኪ ምርቶች እጥረት እና ያልተመጣጠነ የዋጋ ጭማሪ ለሕጉ ተገዢነት ፈተና ሆኗል” ማለታቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።

የአቅርቦት ችግሩን ለመፍታት ባለሀብቶች ወደ ዘርፉ እንዲገቡና ሕብረተሰቡን ለከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ከሚዳርጉ አላስፈላጊ አሠራሮች እንዲቆጥቡ ጥሪ ቀርቧል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0