ፌስታል ላይ የተጣለውን እገዳ ተከትሎ ተኪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያው ለማቅረብ ከሕንድና ቻይና ኩባንያዎች ጋር ውይይት ተጀመረ
14:55 19.02.2026 (የተሻሻለ: 15:04 19.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ፌስታል ላይ የተጣለውን እገዳ ተከትሎ ተኪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለገበያው ለማቅረብ ከሕንድና ቻይና ኩባንያዎች ጋር ውይይት ተጀመረ
ይህም በአዲስ አበባ ከተማ በተተኪ የፌስታል ምርት ግብዓቶች ላይ የታየውን ከፍተኛ የዋጋ ንረት ተከትሎ የመጣ ነው።
ችግሩን ለመቅረፍ ከውጭ አምራች ኩባንያዎች ጋር ንግግር ላይ መሆኑን የከተማዋ የአካባቢ ጥበቃ ባለሥልጣን አስታውቋል።
የባለሥልጣን መሥሪያ ቤቱ ዋና ሥራ አስኪያጅ ዲዳ ድሪባ “በአሁኑ ወቅት በገበያ ላይ ያለው የተተኪ ምርቶች እጥረት እና ያልተመጣጠነ የዋጋ ጭማሪ ለሕጉ ተገዢነት ፈተና ሆኗል” ማለታቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
የአቅርቦት ችግሩን ለመፍታት ባለሀብቶች ወደ ዘርፉ እንዲገቡና ሕብረተሰቡን ለከፍተኛ የዋጋ ጭማሪ ከሚዳርጉ አላስፈላጊ አሠራሮች እንዲቆጥቡ ጥሪ ቀርቧል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X