የሩሲያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በወርቅ ማዕድን ዘርፍ ለመሠማራት ፍላጎት እንዳላቸው ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየሩሲያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በወርቅ ማዕድን ዘርፍ ለመሠማራት ፍላጎት እንዳላቸው ተገለፀ
የሩሲያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በወርቅ ማዕድን ዘርፍ ለመሠማራት ፍላጎት እንዳላቸው ተገለፀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 18.02.2026
ሰብስክራይብ

የሩሲያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በወርቅ ማዕድን ዘርፍ ለመሠማራት ፍላጎት እንዳላቸው ተገለፀ

ኩባንያዎቹ በዘርፉ ትብብር ለመፍጠር አስቻይ ዕድሎችን እየፈተሹ እንደሚገኙ በሞስኮ የኢትዮጵያ አምባሳደር ገነት ተሾመ ለስፑትኒክ ተናግረዋል።

“በእርግጥም የሩሲያ ኩባንያዎች በኢትዮጵያ በማዕድን ዘርፍ በተለይም በወርቅ ማዕድን ማውጣት ላይ ለመሠማራት ፍላጎት አላቸው። በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን እየጎበኙና የትብብር ዕድሎችን እየመረመሩ ይገኛሉ። ሀገራችን ከፍተኛ የወርቅ ክምችት ስላላት እና የውጭ ኩባንያዎችም በኢትዮጵያ የማዕድን ዘርፍ ላይ በንቃት ኢንቨስት እያደረጉ በመሆኑ ይህ ሂደት ተጨባጭ ውጤት እንደሚያመጣ ተስፋ አደርጋለሁ” ብለዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0