መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በሁለት ሳምንታት ውስጥ የሙከራ ትግበራ እንደሚጀመር ተገለፀ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱመሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በሁለት ሳምንታት ውስጥ የሙከራ ትግበራ እንደሚጀመር ተገለፀ
መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በሁለት ሳምንታት ውስጥ የሙከራ ትግበራ እንደሚጀመር ተገለፀ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 18.02.2026
ሰብስክራይብ

መሶብ የአንድ ማዕከል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት በሁለት ሳምንታት ውስጥ የሙከራ ትግበራ እንደሚጀመር ተገለፀ

ይህ አገልግሎት በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና በኦሮሚያ ክልል ሸገር ከተማ ለመጀምሪያ ግዜ ተግባራዊ እንደሚደረግ የፌዴራል መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት አስታውቋል።

የአገልግሎቱ ዳይሬክተር ጄኔራል አንተነህ ማሞ፤ ለሁሉም ማኅበረሰብ ክፍሎች አገልግሎቱን ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ተንቀሳቃሽ አገልግሎት መስጠት አስፈላጊ ሆኖ መገኘቱን ገልፀዋል፡፡

የመሠረተ ልማት ተደራሽነት ዝቅተኛ በሆነባቸው አካባቢዎች ‘በኪዮስክ’ አገልግሎት ለመስጠት ጥናት እየተካሄደ መሆኑንም ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል።

በአሁኑ ወቅት በ23 ተቋምት 187 የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎቶች እየተሰጡ መሆኑን የገለፁት ዳይሬክተር ጄነራሉ፤ በሚቀጥሉት ሦስት ወራት ተቋማትን ወደ 25 በማሳደግ ቅዳሜና እሁድን ጨምሮ 250 አገልግሎቶችን ለመስጠት መታቀዱን ጠቁመዋል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0