“የአፍሪካ የአቪዬሽን አባት” በመባል የሚታወቁት ኢትዮጵያዊው ግርማ ዋቄ፤ የኡጋንዳ አየር መንገድ ጊዜያዊ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
15:16 18.02.2026 (የተሻሻለ: 15:24 18.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
“የአፍሪካ የአቪዬሽን አባት” በመባል የሚታወቁት ኢትዮጵያዊው ግርማ ዋቄ፤ የኡጋንዳ አየር መንገድ ጊዜያዊ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ሆነው ተሾሙ
ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቬኒ፤ ግርማ ዋቄ በአስቸኳይ በአማካሪነት እና እስከ ሐምሌ 2026 ድረስ በተጠባባቂ ዋና ሥራ አስፈፃሚነት እንዲሾሙ ለኡጋንዳ የሥራና የትራንስፖርት ሚኒስትር ካቱምባ ዋማላ መመሪያ ሰጠተዋል።
አንጋፋው የአቪዬሽን ባለሙያ፤ በኡጋንዳ አየር መንገድ ውስጥ ያሉ "በርካታ የአስተዳደር ጉድለቶችን" እንዲያርሙ እና ዋና ሥራ አስፈፃሚ እስኪሾም ድረስ ከቦርዱ ጋር በመተባበር እንዲሠሩ ኃላፊነት ተጥሎባቸዋል።
አቶ ግርማ ዋቄ የኢትዮጵያ አየር መንገድን ለሰባት ዓመታት ያህል መምራታቸው የሚታወስ ነው። አየር መንገዱ በእሳቸው የአመራር ግዜ የአውሮፕላኖቹን ቁጥር እንዲሁም የበርራ መረቡን ያሰፋበት እንደነበር ይነገራል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X