በጄኔቫ ስለተጀመረው የሦስትዮሽ የዩክሬን የሰላም ንግግር እስካሁን የታወቁ መረጃዎች

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱበጄኔቫ ስለተጀመረው የሦስትዮሽ የዩክሬን የሰላም ንግግር እስካሁን የታወቁ መረጃዎች
በጄኔቫ ስለተጀመረው የሦስትዮሽ የዩክሬን የሰላም ንግግር እስካሁን የታወቁ መረጃዎች - Sputnik አፍሪካ, 1920, 17.02.2026
ሰብስክራይብ

በጄኔቫ ስለተጀመረው የሦስትዮሽ የዩክሬን የሰላም ንግግር እስካሁን የታወቁ መረጃዎች

◻ ምክክሩ ለሚዲያ ዝግ ሆኖ የሚካሄድ ሲሆን ለሁለት ቀናት ይቆያል። እንደ ክሬምሊን ቃል አቀባይ ዲሚትሪ ፔስኮቭ ገለጻ፤ እስከ ማክሰኞ መገባደጃ ድረስ ምንም ዓይነት ዝርዝር መረጃ አይጠበቅም።

◻ የሩሲያ ልዑካን ቡድን በፕሬዚዳንቱ ረዳት ሜዲንስኪ የሚመራ ሲሆን ምክትል የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጋሉዚን፣ የወታደራዊ ደህንነት ኃላፊ ኮስቲዩኮቭ እና ሌሎች ባለሥልጣናትን ያካተተ ነው።

◻ እንደ ፔስኮቭ ገለጻ፤ ንግግሩ የግዛት ጥያቄዎችን ጨምሮ ቁልፍ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ያተኩራል።

◻ የዩክሬን የደህንነት እና መከላከያ ምክር ቤት ጸሐፊ ኡሜሮቭ እንደገለጹት፤ አጀንዳው የደህንነት እና ሰብዓዊ ጉዳዮችን ያካትታል።

◻ ኡሜሮቭ ቀደም ሲል ኪዬቭ በጄኔቫው ስብሰባ ላይ የ "ኢነርጂ ተኩስ አቁም" ሃሳብ እንደምታነሳ ተናግረው ነበር።

◻ የእንግሊዝ ልዑካን ቡድን በስብሰባው ቦታ አቅራቢያ የታየ ሲሆን የስፑትኒክ ምንጭ ልዑኩ ስለ ንግግሩ ውጤት መረጃ ለማግኘት ጥረት እንደሚያደርግ ገልጸዋል።

◻ የእንግሊዝ ልዑካን ቡድንን የሚመሩት የስታርመር የደህንነት አማካሪ፤ በጄኔቫ ከአሜሪካ ልዑካን ቡድን አባላት ጋር ቀደም ብለው ስብሰባ አካሂደዋል።

◻ ንግግሩ በሩሲያኛ እና እንግሊዝኛ ቋንቋዎች እየተካሄደ ይገኛል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0