ኢትዮጵያ የታጁራ ወደብን ለተጨማሪ ወጪ እና ገቢ ንግድ በአማራጭነት ለመጠቀም ያለመ ውይይት ከጅቡቲ ጋር አካሄደች
16:03 17.02.2026 (የተሻሻለ: 16:44 17.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ የታጁራ ወደብን ለተጨማሪ ወጪ እና ገቢ ንግድ በአማራጭነት ለመጠቀም ያለመ ውይይት ከጅቡቲ ጋር አካሄደች
በትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ የተመራ ልዑክ ቡድን በታጁራ አጠቃቀም ዙሪያ ከወደቡ አስተዳዳሪዎች ጋር ውይይት አድርጓል፡፡
በውይይቱም የታጁራ ወደብን አቅም በማሳደግ እና በመጠቀም የአፈር ማዳበሪያ ወደ ኢትዮጵያ ስለማስገባት ምክክር መደረጉን ሚኒስቴሩ አስታውቋል።
ሚኒስትር ዓለሙ ስሜ፤ ወደቡን ሙሉ በሙሉ ወደ ሥራ ማስገባት የየብስ ርቀትን በ60 ኪሎ ሜትር እንደሚቀንስ እና የሎጅስቲክስ ዘርፉን እንደሚያፋጥን ተናግረዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

