የጋናው ፕሬዝዳንት የአፍሪካን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድ በሕብረቱ ጉባኤ ላይ ጥሪ አቀረቡ
20:11 16.02.2026 (የተሻሻለ: 20:14 16.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የጋናው ፕሬዝዳንት የአፍሪካን የኢኮኖሚ ሉዓላዊነት ለማረጋገጥ አስቸኳይ እርምጃ እንዲወሰድ በሕብረቱ ጉባኤ ላይ ጥሪ አቀረቡ
በአዲስ አበባ ከተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ ጎን ለጎን በተዘጋጀው "አክራ ሪሴት" በተሰኘ መድረክ ላይ ንግግር ያደረጉት ጆን ድራማኒ ማሃማ፣ የአፍሪካ መሪዎች ከረጅም ውይይቶች ወጥተው ዋና ዋና አኅጉራዊ ማዕቀፎችን ወደ ተግባር እንዲቀይሩ አሳስበዋል።
ማሃማ ያቀረቧቸው ዋና ዋና ሃሳቦች፦
ከግጭት ነፃ የሆኑ ማዕድናት ማረጋገጫ ሥርዓት መዘርጋት፣
የአኅጉሪቱን የተፈጥሮ ሀብቶች እሴት የማሳደግ ሥራን ማጠናከር እና
የአኅጉር ውስጥ ንግድን ለማቀላጠፍ ፓን-አፍሪካን የክፍያ እና የፋይናንስ ሥርዓቶችን ማጠናከር።
የአፍሪካ ዕድገት ተወዳዳሪ በሆኑ የአገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች፣ ግልጽ በሆነ የሀብት አስተዳደር እና ጠንካራ የንግድ ትስስር ላይ የተመሠረተ መሆን እንዳለበት ፕሬዝዳንቱ አጽንኦት ሰጥተዋል።
እንደ ባለሥልጣናት ገለጻ፣ የ"አክራ ሪሴት" ተነሳሽነት በራስ መተማመንን፣ የኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽንን እና በአባል ሀገራት መካከል ስትራቴጂካዊ ኢኮኖሚያዊ ትብብርን ማስፈን ላይ ትኩረት ያደርጋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X