#viral | የናይጄሪያው አርጉንጉ የዓሳ ማጥመድ ፌስቲቫል ከዓመታት መቋረጥ በኋላ በድል ተመለሰ
19:29 16.02.2026 (የተሻሻለ: 19:34 16.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
#viral | የናይጄሪያው አርጉንጉ የዓሳ ማጥመድ ፌስቲቫል ከዓመታት መቋረጥ በኋላ በድል ተመለሰ
ይህ ዓለም አቀፍ ፌስቲቫል በዚህ ሳምንት መጨረሻ በድል አድራጊነት የተመለሰ ሲሆን፣ በአስር ሺዎች የሚቆጠሩ ዓሳ አጥማጆች በኬቢ ግዛት በሚገኘው የማታ ፋዳን ወንዝ ላይ በመገኘት በባህላዊ መረቦች፣ በቅል እና በባዶ እጃቸው በውድድሩ ተሳትፈዋል።
ታላቁ ማስገር
አሸናፊው አቡበከር ኡስማን 59 ኪሎ ግራም የሚመዝን ግዙፍ ዓሳ በማጥመድ የሁለት መኪናዎች፣ የገንዘብ እና የሌሎች ሽልማቶች ባለቤት ሆኗል።
ሁለተኛ የወጣው ተወዳዳሪ አንድ መኪና፣ የሐጅ ጉዞ ዕድል እና የገንዘብ ሽልማት ሲያገኝ፤ ሦስተኛው ደግሞ ሁለት ሞተር ብስክሌቶች እና የገንዘብ ሽልማት ተረክቧል።
በቦታው የተገኙት ፕሬዝዳንት ቦላ ቲኑቡ፣ የፌስቲቫሉ መመለስ ከዓመታት የደህንነት ችግር በኋላ በአካባቢው አስተማማኝ መረጋጋት መስፈኑን የሚያሳይ ማረጋገጫ ነው ብለዋል።
ይህ ፌስቲቫል ለመጀመሪያ ጊዜ የተካሄደው እ.ኤ.አ. በ1934 በሶኮቶ ካሊፌት እና በአርጉንጉ ኤሚሬት መካከል ሰላም መውረዱን ለማብሰር ሲሆን፣ እስከ ጎርጎሮሳውያኑ 2010 ድረስ ያለማቋረጥ ሲካሄድ ቆይቷል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X