ፕሬዝዳንት ታዬ፣ በዚህ አስርት ዓመት ወደ ሥራ እድሜ ክልል የሚገቡ 362 ሚሊዮን ወጣቶች “የአፍሪካ ታላቅ ጥንካሬ ሊሆኑ ይችላል" አሉ

ሰብስክራይብ

ፕሬዝዳንት ታዬ፣ በዚህ አስርት ዓመት ወደ ሥራ እድሜ ክልል የሚገቡ 362 ሚሊዮን ወጣቶች “የአፍሪካ ታላቅ ጥንካሬ ሊሆኑ ይችላል" አሉ

በአኅጉሪቱ በአግሮ-ፕሮሰሲንግ፣ በትራንስፖርት፣ በአገልግሎት ዘርፍ፣ በእሴት ሰንሰለት ልማት፣ በማኑፋክቸሪንግ እና በአይሲቲ የአፍሪካ የእድገት ሞዴል እያበበ ቢሆንም የሥራ ዕድልን በመፍጠር ረገድ ብዙ እንደሚቀራት ታዬ አጽቀሥላሴ ተናግረዋል፡፡

“ምንም እንኳን ይህ እድገት ቢኖርም፣ [...] በተለይም በወጣት ወንዶችና ሴቶች በሚመሩ የንግድ ሥራዎች ላይ ከፍተኛ ክፍተት ገጥሟታል፡፡” ሲሉ በአዲስ አበባ መካሄድ በጀመረው 9ኛው የአፍሪካ ቢዝነስ ፎረም ላይ ተናግረዋል፡፡

ፕሬዝዳንት ታዬ፣ በዚህ አስርት ዓመት ውስጥ 362 ሚሊዮን ወጣቶች ወደ ሥራ እድሜ ክልል እንደሚገቡ ጠቁመው አሁን ያለው የሥራ ገበያ ግን 151 ሚሊየን ብቻ ሊወስድ መቻሉን አሳስበዋል፡፡

"ወጣቶቻችንን ወደ አምራች ካፒታል እና ፈጠራችንን ወደ የሰለጠነ ኢንተርፕራይዞች ለመቀየር ከተሳካልን ይህ የሥነ–ሕዝብ አወቃቀር እውነታ የአፍሪካ ታላቅ ጥንካሬ ሊሆን ይችላል" ብለዋል፡፡

ትራንስፎርሜሽን ረቂቅ ሐሰተኛ ቃል ኪዳን ሆኖ ሊቆይ አይችልም ያሉት ፕሬዝዳንቱ ተሰጥኦን ወደ ሰው ካፒታል የሚቀይሩ ኢንቨስትመንቶች ውስጥ መታየት አለበት በማለት መናገራቸውን የስፑትኒክ አፍሪካ ጋዜጠኛ ዘግቧል፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0