ኢትዮጵያ የቡና መማማሪያ ማዕከል ሥራ አስጀመረች

ሰብስክራይብ

ኢትዮጵያ የቡና መማማሪያ ማዕከል ሥራ አስጀመረች

ማዕከሉ በይዘት ደረጃ ቡና ከዘር እስከ ወጪ ንግድ ድረስ ምን እንደሚመስል እውቀትና ክህሎት ማስጨበጫ ማዕከል እንደሚሆን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን አስታውቋል፡፡

የማዕከሉ ትኩረቶች፦

የኢትዮጵያ ቡና ታሪክ፣

የሴቶች ሚና በቡናው ዘርፍ፣

ቡና ለኢኮኖሚና ማኅበራዊ ሕይወት ያሉት ጠቀሜታዎችን እና

ሌሎች የባሕልና የትምህርት ርዕሰ ጉዳዮች

ዓለም አቀፍ ርዕይ፦ የቡና ሁለንተናዊ ጉዳይ ለዓለም የሚተዋወቅበት ማዕከል የመሆን ግብም ተቀምጦለታል።

በትናትናው ዕለት ተመረቆ የተከፈተው የማዕከሉ እንቅስቃሴ የመጀመሪያው ምዕራፍ ሲሆን ቀጣዩ ምዕራፍ ዲጂታላይዝ ማድረግ መሆኑ ተገልጿል፡፡

ሁለቱንም ማዕከሉን የማደራጀት ምዕራፎች እየሰራ የሚገኘው በአገር በቀል ድርጅት እንደሆነ ባለሥልጣኑ ገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0