ቀጣዩ የተመድ ዋና ጸሐፊ ምርጫ ለአፍሪካ ለምን አስፈላጊ ሆነ?- የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምልከታቸውን አጋርተዋል
ቀጣዩ የተመድ ዋና ጸሐፊ ምርጫ ለአፍሪካ ለምን አስፈላጊ ሆነ?- የላይቤሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ምልከታቸውን አጋርተዋል
የአፍሪካ ቀዳሚ ፍላጎት ግጭቶችን መከላከል የሚችል፣ ፈጣን ምላሽ የሚሰጥ እና የወደፊት ቀውሶችን ለማስቆም የተቀናጁ የሰላም ስልቶችን በወቅቱ መገንባት የሚችል የተባበሩት መንግስታት መሪ ማግኘት ነው ሲሉ ሳራ ፍራንሲስ ቤይሶሎው ኒያንቲ በአዲስ አበባ ከተካሄደው 39ኛው የአፍሪካ ሕብረት የመሪዎች ጉባኤ ጎን ለጎን ለስፑትኒክ አፍሪካ ገልጸዋል።
ሚኒስትሯ ያነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች፦
ስለ ተባበሩት መንግስታት እና ተቋማዊ ማሻሻያ - በአሁኑ ወቅት እየተካሄዱ ያሉ የለውጥ ውይይቶች፣ለምሳሌ፣ የድርጅቱን ኤጀንሲዎች ማዋሃድ በቂ አይደሉም። አፍሪካ በተግባር የሚታይ እና መሰረታዊ ለውጥን በመሬት ላይ ማምጣት የሚችል ራዕይና ስልጣን ያለው ዋና ጸሐፊ ያስፈልጋታል።
አጋርነትን በተመለከተ፦ ኒያንቲ አፍሪካ የምትፈልገው "ምጽዋት ወይም እርዳታ" እንዳልሆነ አጽንኦት ሰጥተዋል። ምንም እንኳን እርዳታ ለሰብአዊ ቀውሶች ያለውን ሚና ብታምንም፣ አፍሪካ የምትፈልገው ኢንቨስትመንት እና የጋራ ተጠቃሚነትን የሚያረጋግጥ እኩል አጋርነት ነው። "ልማት ከሌለ ሰላምና ደህንነት ዘላቂ ሊሆኑ አይችሉም" በማለት ሥራ የሚፈጥር አጋርነት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል።
ስለ አፍሪካ አንድነት፦ የአፍሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እና ባለሙያዎች "የፈቃደኞች ጥምረት" በመፍጠር ኤ3 ተብለው የሚጠሩትን (ላይቤሪያ፣ ሶማሊያ እና ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ) በመደገፍ ላይ ናቸው። ይህም አፍሪካ ለዋና ጸሐፊው ምርጫ ያላትን የጋራ መስፈርት ለመቅረጽ እና የባለብዙ ወገን ግንኙነትን ወደ አኅጉሪቱ እውነተኛ ፍላጎቶች ለመምራት ያለመ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X