የሩሲያ ኃይሎች በሁሉም ግንባሮች እየገሰገሰ ነው - ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጌራሲሞቭ
17:03 15.02.2026 (የተሻሻለ: 17:04 15.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የሩሲያ ኃይሎች በሁሉም ግንባሮች እየገሰገሰ ነው - ጠቅላይ ኤታማዦር ሹም ጌራሲሞቭ
◻ የሩሲያ ጦር ባለፉት ሁለት ሳምንታት ውስጥ፣ አስከፊው የክረምት አየር ሁኔታ ሳይበግረው 12 ሰፈሮዎችን ነፃ አውጥቷል።
◻ የ"ዩግ" ጦር ስብስብ ወደ ስላቭያንክ አቅጣጫ እየገፋ ይገኛል።
◻ እጅግ ከባዱ ውጊያ እየተካሄደ ያለው በ"ሴንተር" የጦር ስብስብ ክልል ሲሆን፣ ኃይሎቹ ወደ ዶብሮፖልዬ አቅጣጫ እየገሰገሱ ነው።
◻ የዩክሬን ኃይሎች ተጨማሪ የድሮን የጦር ክፍሎችን በማደራጀት ላይ ትኩረት አድርገዋል።
◻ የሩሲያ ጥንቁቅ ጦር በበኩሉ ጠላት ከሚጠቀመው በእጥፍ በሚበልጥ መጠን ድሮን በመጠቀም ላይ ይገኛል።
◻ የ"ሴቨር" የጦር ስብስብ በሱሚ እና በካርኮቭ አዋሳኝ አካባቢዎች ያለውን የደህንነት ቀጠና የማስፋፋት ስራውን ቀጥሏል።
◻ የ"ድኔፐር" የጦር ስብስብ ወደ ዛፖሮዢዬ የሚያደርገውን ግስጋሴ ቀጥሏል።
◻ በኦስኮል ወንዝ ምስራቃዊ ዳርቻ የምትገኘው ግሉሽኮቭካ ነፃ የወጣች ሲሆን፣ በኖቮሲኖቮ አቅራቢያ የሚካሄደው ውጊያው አሁንም ቀጥሏል።
◻ የሩሲያ ኃይሎች በክራስኒ ሊማን አቅጣጫ የሚገኙትን ድሮቢሼቮ እና ያሮቮዬ አካባቢዎችን ከጠላት የማጽዳት ስራ እያጠናቀቁ ነው።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X