ኒጀር እና አልጄሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ወደ ነበረበት መለሱ
19:19 13.02.2026 (የተሻሻለ: 19:24 13.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኒጀር እና አልጄሪያ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነታቸውን ወደ ነበረበት መለሱ
የአልጄሪያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ በሀገሪቱ ፕሬዝዳንት ትዕዛዝ በኒጀር የሚገኘው አምባሳደር ወዲያውኑ ወደ ስራቸው እንዲመለሱ ተደርጓል።
ይህ ውሳኔ የተላለፈው በትናንትናው ዕለት በአልጄሪያ የሚገኘው የኒጀር አምባሳደር ወደ አልጀርስ ተመልሰው ስራቸውን መጀመራቸውን ተከትሎ መሆኑን መግለጫው አመልክቷል።
የአምባሳደሮቹ መመለስ በሁለቱ ሀገራት መካከል ያለውን ከፍተኛ የሁለትዮሽ የፖለቲካ ውይይት እንደገና ለማስጀመር ያለመ መሆኑም ተገልጿል።
ኒጀር እና የሳሕል አጋሮቿ አምባሳደሮቻቸውን ጠርተው የነበረው ባለፈው ዓመት ሚያዝያ ወር የአልጄሪያ ጦር የማሊን ድሮን መትቶ ከጣለ በኋላ ነበር። በወቅቱ አልጄሪያም በምላሹ አምባሳደሯን ከኒያሜ ጠርታ እንደነበር ይታወሳል።
በሰው ሠራሽ አስተውሎት የበለፀገ ምስል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X