ለአፍሪካ የሰላም እና ልማት ችግር ዋነኛው መንስኤ የውጭ ጣልቃ ገብነት ነው - የምዕራባዊ ሰሃራ* ተወካይ

ሰብስክራይብ

ለአፍሪካ የሰላም እና ልማት ችግር ዋነኛው መንስኤ የውጭ ጣልቃ ገብነት ነው - የምዕራባዊ ሰሃራ* ተወካይ

የአፍሪካ አገራት ለአፍሪካ ሁለንተናዊ ዕድገት እንቅፋት የሆኑ የውጭ ኃይሎችን ጣልቃ ገብነት በትብብር መመከት እንዳለባቸው መሀመድ ያስለም ቤይሳት፣ 48ኛው የአፍሪካ ኅብረት የሥራ አስፈጻሚ ምክር ቤት መደበኛ ስብሰባ ጎን ለጎን ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ገልጸዋል።

"በተለይ ኃላፊነት የጎደላቸው የውጭ አካላት በውስጥ ጉዳያችን ገብተው አለመረጋጋት፣ መከፋፈል እና በምድራችን የማይገቡ ነገሮችን እንዲያደርጉ ከመጋበዝ መቆጠብ አለብን።" ሲሉ ተወካዩ አክለዋል።

* የክልሉ ነፃነት፣ የሰሃራዊ አረብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክን ባወጀው የፖሊሳሪዮ ግንባር ግፊት የሆነ ነው። በአንጻሩ ሞሮኮ ምዕራባዊ ሰሃራን የግዛቷ ዋና አካል አድርጋ ትመለከታታለች፡፡

እ.አ.አ በ1982 የቀደሞ የአፍሪካ አንድነት ድርጀት (የአሁኑ የአፍሪካ ሕብረት) ሰሃራዊ አረብ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክን በአባልነት የተቀበላት ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የሕብረቱ ንቁ አባል ናት፡፡

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0