የካሳ ክፍያ ጥያቄ ዓለም አቀፋዊ መነቃቃት እያገኘ ነው፤ የቅኝ ገዥ ኃይሎችም ከዚህ እውነት ጋር መታረቅ አለባቸው - የታሪክ ባለሙያ

ሰብስክራይብ

የካሳ ክፍያ ጥያቄ ዓለም አቀፋዊ መነቃቃት እያገኘ ነው፤ የቅኝ ገዥ ኃይሎችም ከዚህ እውነት ጋር መታረቅ አለባቸው - የታሪክ ባለሙያ

​"ቅርሶችን መመለስ ትንሽ እርምጃ እንጂ የጉዳዩ ፍጻሜ አይደለም" ሲሉ በናይሮቢ የዩናይትድ ስቴትስ ዓለም አቀፍ ዩኒቨርሲቲ የታሪክ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ፕሮፌሰር የሆኑት ማቻሪያ ሙኔኔ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። ፕሮፌሰሩ ይህንን ያሉት የካምብሪጅ ዩኒቨርሲቲ ሙዚየም ከናይጄሪያ የተዘረፉ 116 የናስ ቅርሶችን ለመመለስ የወሰነውን ውሳኔ አስመልክቶ በሰጡት አስተያየት ነው።

​ የአፍሪካ ቅርሶችን ወደ ሀገራቸው ለመመለስ ዋናው እንቅፋት የቅኝ ገዥ ኃይሎች የፈጸሟቸውን ወንጀሎች ለማመን ፈቃደኛ አለመሆናቸው ነው ያሉት ፕሮፌሰር ሙኔኔ፤ በተለይም የቅኝ አገዛዝ ወንጀሎችን እውነታ የሚቃወመው የ "ኒው ራይት" ንቅናቄ መነሳትን እንደ ትልቅ ችግር ጠቅሰዋል።

​ ፕሮፌሰር ሙኔኔ እነዚህ ተግዳሮቶች ቢኖሩም፣ የአፍሪካ ሀገራት የቅኝ ገዥ ኃይሎችን ለፈጸሙት ድርጊት ተጠያቂ ለማድረግ የካሳ ክፍያ ጥያቄያቸውን አጠናክረው እንዲቀጥሉ አሳስበዋል።

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0