ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከእንስሳት አጥንት የአፈር ማዳበሪያ ማምረቱን ይፋ አደረገ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱጅማ ዩኒቨርሲቲ ከእንስሳት አጥንት የአፈር ማዳበሪያ ማምረቱን ይፋ አደረገ
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከእንስሳት አጥንት የአፈር ማዳበሪያ ማምረቱን ይፋ አደረገ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 12.02.2026
ሰብስክራይብ

ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከእንስሳት አጥንት የአፈር ማዳበሪያ ማምረቱን ይፋ አደረገ

ቦንቻር የሚል መጠሪያ የተሰጠው ይህ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ውጤታማነቱ በሙከራ እንደተረጋገጠ እና ለአፈር ማዳበሪያ የሚወጣውን 52 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስቀር ዩኒቨርስቲው አስታውቋል፡፡

“ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባው ማዳበሪያ በዓለም ገበያ ዋጋው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ እና ክምችቱም እጅግ እየተመናመነ በመሆኑ ሀገር በቀል መፍትሄ ያስፈልጋል በሚል ወደ ሥራ ገብተናል” ሲሉ የጅማ ዩኒቨርስቲ ግብርናና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ ውስጥ መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ሚልኪያስ አህመድ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡

ከተለያዩ የእንሣት አጥንቶች የሚመረተው ማዳበሪያ፤ ለሰብል ከሚሰጠው ጠቀሜታ በተጨማሪ በአፈር ውስጥ የሚገኘውን አሲድ ለማሻሻል ጠቃሚ ሆኖ መገኘቱን ገልፀዋል፡፡

በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0