ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከእንስሳት አጥንት የአፈር ማዳበሪያ ማምረቱን ይፋ አደረገ
17:32 12.02.2026 (የተሻሻለ: 17:34 12.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከእንስሳት አጥንት የአፈር ማዳበሪያ ማምረቱን ይፋ አደረገ
ቦንቻር የሚል መጠሪያ የተሰጠው ይህ የተፈጥሮ ማዳበሪያ ውጤታማነቱ በሙከራ እንደተረጋገጠ እና ለአፈር ማዳበሪያ የሚወጣውን 52 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስቀር ዩኒቨርስቲው አስታውቋል፡፡
“ወደ ሀገር ውስጥ የሚገባው ማዳበሪያ በዓለም ገበያ ዋጋው ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ እና ክምችቱም እጅግ እየተመናመነ በመሆኑ ሀገር በቀል መፍትሄ ያስፈልጋል በሚል ወደ ሥራ ገብተናል” ሲሉ የጅማ ዩኒቨርስቲ ግብርናና እንስሳት ህክምና ኮሌጅ ውስጥ መምህር እና ተመራማሪ የሆኑት ዶ/ር ሚልኪያስ አህመድ ለሀገር ውስጥ ሚዲያ ተናግረዋል፡፡
ከተለያዩ የእንሣት አጥንቶች የሚመረተው ማዳበሪያ፤ ለሰብል ከሚሰጠው ጠቀሜታ በተጨማሪ በአፈር ውስጥ የሚገኘውን አሲድ ለማሻሻል ጠቃሚ ሆኖ መገኘቱን ገልፀዋል፡፡
በሰው ሠራሽ አስተውህሎት የበለፀገ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X