የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያውያን ላይ የጣለው የጉዞ እገዳ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ገቢ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩ ተገለፀ
16:16 11.02.2026 (የተሻሻለ: 16:24 11.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአሜሪካ መንግሥት በኢትዮጵያውያን ላይ የጣለው የጉዞ እገዳ በኢትዮጵያ አየር መንገድ ገቢ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩ ተገለፀ
በጉዞ እገዳ ምክንያት ወደ አሜሪካ ከተሞች የሚጓዙ መንገደኞች ቁጥር መቀነሱን የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው ትናንት የ6 ወር አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት ተናግረዋል።
“የአሜሪካ መንግሥት በየጊዜው ከጉዞ ጋር በተያያዘ የሚያወጣቸው እገዳዎች ወደ አሜሪካ ከተሞች በሚጓጓዙ መንገደኞቻችን ላይ ተጽዕኖ አሳድሮብናል” ብለዋል፡፡
ከየካቲት እስከ ግንቦት ባሉት አራት ወራት ውስጥ ወደ አሜሪካ የሚጓዙ መንገደኞች ቁጥር እንደሚቀንስ ቢጠበቅም፤ የአሜሪካ መንግሥት በየጊዜው የሚጥላቸው የቪዛ እና ጉዞ ገደቦች ግን ችግሩን አባብሶታል ማለታቸውን ጠቅሶ የሀገር ውስጥ ሚዲያ ዘግቧል።
አሜሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ ለ75 ሀገራት ዜጎች የፍልሰት ቪዛ መስጠት እንደምታቆም የሀገሪቱ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ባለፈው ጥር ወር ማስታወቁ ይታወሳል፡፡
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X