ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ለምግብ ዋስትና እና ለኑሮ ማሻሻያ የሚውል የ71.9 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራረሙ
14:53 11.02.2026 (የተሻሻለ: 14:54 11.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
ኢትዮጵያ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ ለምግብ ዋስትና እና ለኑሮ ማሻሻያ የሚውል የ71.9 ሚሊዮን ዶላር ስምምነት ተፈራረሙ
ከገንዘብ ድጋፍ ስምምነቱ 25.64 ሚሊዮኑ በዕርዳታ፤ ቀሪው 46.30 ሚሊዮን ዶላር በብድር መልክ የቀረበ መሆኑን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።
የስምምነቱ ዋነኛ ዓላማዎች፦
የአርብቶ እና ከፊል አርብቶ አደር አካባቢ ማኅበረሰቦች የአየር ንብረት ለውጥ የሚያስከትለውን ተጋላጭነት እንዲቋቋሙ ማስቻል።
የአየር ንብረት ለውጥን ያገናዘቡ የፈጠራ ሥራዎችን፣ የዲጂታል የምክር አገልግሎቶችን እና የአየር ንብረት ፋይናንስ ተደራሽነትን ማቀናጀት።
የውሃ መሠረተ ልማቶች፣ የማኅበረሰብ መስኖ ልማት፣ የእንስሳት መገልገያ ተቋማት እና የታዳሽ ኃይል አማራጮችን ማስፋፋት።
ስምምነቱን የገንዘብ ሚኒስትር አሕመድ ሽዴ እና የአፍሪካ ልማት ባንክ የምስራቅ አፍሪካ ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር አሌክስ ሙቢሩ ተፈራርመዋል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X