በቀጣይ ስድስት ወራት ከ1 ሺህ 200 በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ ተባለ
15:39 10.02.2026 (የተሻሻለ: 15:44 10.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በቀጣይ ስድስት ወራት ከ1 ሺህ 200 በላይ ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ይገነባሉ ተባለ
በመላ ሀገሪቱ በሚገኙና ምንም አይነት ቅድመ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በሌላቸው 626 ወረዳዎች አንድ አንድ ትምህርት ቤት እንደሚገነባ ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ አስታውቀዋል።
በተጨማሪም በዚህ ሀገራዊ ፕሮጀክት ተጠቃሚ የሚሆኑ ክልሎች እና የከተማ መስተዳድሮች በየወረዳው በሚገነባው ትምህርት ቤት ተመሳሳይ ሌላ ትምህርት ቤት እንዲገነቡ እንደሚጠበቅባቸው አስገንዝበዋል፡፡
የትምህርት ቤቶቹ ዲዛይን ተሠርቶ መጠናቀቁን የጠቆሙት ሚኒስትሩ፣ በቀጣይ ከክልሎች ጋር በመሆን ኮንትራክተሮችን በመለየት ግንባታው በፍጥነት እንደሚጀመር ገልጸዋል።
ባለፉት ዓመታት ከ34 ሺህ በላይ ቅድመ አንደኛ ትምህር ቤቶች በሀገር አቀፍ ደረጃ መገንባታቸውን የትምህርት ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X