በሩሲያው ጄኔራል አሌክሼቭ የግድያ ሴራ ላይ የተሳተፈ ተጨማሪ ግብረ-አብር በቁጥጥር ስር ዋለ
15:16 10.02.2026 (የተሻሻለ: 15:24 10.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
በሩሲያው ጄኔራል አሌክሼቭ የግድያ ሴራ ላይ የተሳተፈ ተጨማሪ ግብረ-አብር በቁጥጥር ስር ዋለ
ግለሰቡ ቀደም ሲል በሞስኮ በቁጥጥር ስር የዋለው የሌላኛው ተባባሪ ልጅ መሆኑን የሩሲያ የፌዴራል ደኅንነት አገልግሎት ለስፑትኒክ አስታውቋል።
እንደ አገልግሎቱ መግለጫ፤ ግለሰቡ ለቡድኑ የስለላ ሥራ በመሥራት፣ ተሽከርካሪ በማቅረብ፣ የመኪና ካሜራ እና የአቅጣጫ ጠቋሚ (ጂ.ፒ.ኤስ) መከታተያ መሣሪያዎችን በማዘጋጀት ድጋፍ አድርጓል።
በቁጥጥር ስር የዋለው ግለሰብ በሰጠው የዕምነት ክህደት ቃል፤ የስለላ ተግባሩ ጄኔራል አሌክሼቭን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ሁለት የመከላከያ ሚኒስቴር ሠራተኞችንም ኢላማ ያደረገ እንደነበር ይፋ አድርጓል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X