በጊኒ ዋና ከተማ ከሚገኝ ዋና እስር ቤት አቅራቢያ የተኩስ ድምፅ ተሰማ
15:11 10.02.2026 (የተሻሻለ: 15:14 10.02.2026)
© telegram sputnik_ethiopia
ሰብስክራይብ
በጊኒ ዋና ከተማ ከሚገኝ ዋና እስር ቤት አቅራቢያ የተኩስ ድምፅ ተሰማ
በኮናክሪ ማዕከላዊ እስር ቤት አቅራቢያ ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት የተሰማው ተኩስ በከተማው መሃል ከፍተኛ ትርምስ መፍጠሩን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።
የአይን እማኞች እስረኞችን የማስመለጥ ወይም የማስውጣት ሙከራ ሊሆን እንደሚችል ማመልከታቸውን ዘገባዎቹ ጨምረው ገልጸዋል።
የፀጥታ ኃይሎች ወደ ከተማው መሃል የሚወስዱ መንገዶችን የዘጉ ሲሆን አካባቢውን በታጠቁ ተሽከርካሪዎች በመጠበቅ ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል። እስካሁን ከመንግሥት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ የለም።
ከማኅበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘ ተንቀሳቃሽ ምሥል
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X