በጊኒ ዋና ከተማ ከሚገኝ ዋና እስር ቤት አቅራቢያ የተኩስ ድምፅ ተሰማ

ሰብስክራይብ

በጊኒ ዋና ከተማ ከሚገኝ ዋና እስር ቤት አቅራቢያ የተኩስ ድምፅ ተሰማ

በኮናክሪ ማዕከላዊ እስር ቤት አቅራቢያ ዛሬ ማክሰኞ ጠዋት የተሰማው ተኩስ በከተማው መሃል ከፍተኛ ትርምስ መፍጠሩን የአካባቢው መገናኛ ብዙኃን ዘግበዋል።

የአይን እማኞች እስረኞችን የማስመለጥ ወይም የማስውጣት ሙከራ ሊሆን እንደሚችል ማመልከታቸውን ዘገባዎቹ ጨምረው ገልጸዋል።

የፀጥታ ኃይሎች ወደ ከተማው መሃል የሚወስዱ መንገዶችን የዘጉ ሲሆን አካባቢውን በታጠቁ ተሽከርካሪዎች በመጠበቅ ላይ እንደሚገኙ ተነግሯል። እስካሁን ከመንግሥት የተሰጠ ይፋዊ መግለጫ የለም።

ከማኅበራዊ ትስስር ገፅ የተገኘ ተንቀሳቃሽ ምሥል

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0