የአፋሮችን ባሕላዊ ሕግ ለማዋሃድ ያለመ ውይይት በሰመራ ተካሄደ

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱየአፋሮችን ባሕላዊ ሕግ ለማዋሃድ ያለመ ውይይት በሰመራ ተካሄደ
የአፋሮችን ባሕላዊ ሕግ ለማዋሃድ ያለመ ውይይት በሰመራ ተካሄደ - Sputnik አፍሪካ, 1920, 10.02.2026
ሰብስክራይብ

የአፋሮችን ባሕላዊ ሕግ ለማዋሃድ ያለመ ውይይት በሰመራ ተካሄደ

በጂቡቲ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዋና ፀሐፊ ናጂብ አብደላ መሐመድ ካሚል የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በውይይቱ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡

የጋራ ውይይቱ በኢትዮጵያ፣ በጂቡቲ እና በኤርትራ የአፋር ማኅበረሰቦች ዘንድ ወጥ የሆነ የባሕላዊ ሕግ ማዕቀፍ ለመዘርጋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።

የመድረኩ ትኩረት "አፋሬ ማድዓ" የተሰኘውን የአፋር ሕዝብ የጋራ ባሕላዊ የፍትሕ ስርዓት በአማራጭ የግጭት አፈታት መፍትሄነት ጥቅም ላይ ማዋል በሚቻልበት አግባብ ላይ መወያየት ነው፡፡

በሌላ በኩል፤ "አፋሬ ማድዓን" በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት በማይዳሰሱ የዓለም ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ማስመዝገብም የውይይቱ አጀንዳ ነው።

"አፋሬ ማድዓ" ከፍትሕ ስርዓትነት ባለፈ ለዘመናት የዘለቀ የሰላም፣ የዕርቅ እና የማኅበራዊ ትስስር ዋልታ ሆኖ ያገለገለ ጥበብ እንደሆነ በመድረኩ ላይ ተገልጿል።

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
የአፋሮችን ባሕላዊ ሕግ ለማዋሃድ ያለመ ውይይት በሰመራ ተካሄደ - Sputnik አፍሪካ
1/2
© telegram sputnik_ethiopia / ወደ ፎቶ ባንክ ይሂዱ
የአፋሮችን ባሕላዊ ሕግ ለማዋሃድ ያለመ ውይይት በሰመራ ተካሄደ - Sputnik አፍሪካ
2/2
1/2
2/2
አዳዲስ ዜናዎች
0