የአፋሮችን ባሕላዊ ሕግ ለማዋሃድ ያለመ ውይይት በሰመራ ተካሄደ
14:24 10.02.2026 (የተሻሻለ: 14:34 10.02.2026)

© telegram sputnik_ethiopia
/ ሰብስክራይብ
የአፋሮችን ባሕላዊ ሕግ ለማዋሃድ ያለመ ውይይት በሰመራ ተካሄደ
በጂቡቲ የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ዋና ፀሐፊ ናጂብ አብደላ መሐመድ ካሚል የተመራ ከፍተኛ የልዑካን ቡድን በውይይቱ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል፡፡
የጋራ ውይይቱ በኢትዮጵያ፣ በጂቡቲ እና በኤርትራ የአፋር ማኅበረሰቦች ዘንድ ወጥ የሆነ የባሕላዊ ሕግ ማዕቀፍ ለመዘርጋት ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
የመድረኩ ትኩረት "አፋሬ ማድዓ" የተሰኘውን የአፋር ሕዝብ የጋራ ባሕላዊ የፍትሕ ስርዓት በአማራጭ የግጭት አፈታት መፍትሄነት ጥቅም ላይ ማዋል በሚቻልበት አግባብ ላይ መወያየት ነው፡፡
በሌላ በኩል፤ "አፋሬ ማድዓን" በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት በማይዳሰሱ የዓለም ቅርሶች ዝርዝር ውስጥ ማስመዝገብም የውይይቱ አጀንዳ ነው።
"አፋሬ ማድዓ" ከፍትሕ ስርዓትነት ባለፈ ለዘመናት የዘለቀ የሰላም፣ የዕርቅ እና የማኅበራዊ ትስስር ዋልታ ሆኖ ያገለገለ ጥበብ እንደሆነ በመድረኩ ላይ ተገልጿል።
ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

