ዓለም ወደ 'ባለብዝሃ-ዋልታነት' እየተሸጋገረ ባለበት በዚህ ወቅት በአፍሪካ 'በጣም አስገራሚ ለውጦች' እየታዩ ነው - ላቭሮቭ

ሰብስክራይብ

ዓለም ወደ 'ባለብዝሃ-ዋልታነት' እየተሸጋገረ ባለበት በዚህ ወቅት በአፍሪካ 'በጣም አስገራሚ ለውጦች' እየታዩ ነው - ላቭሮቭ

አፍሪካውያን ቀደም ሲል በሶቪየት ኅብረት ይደገፍ የነበረውን፤ ጥሬ ሀብትን ብቻ ወደ ውጭ መላክን በማቆም የራሳቸውን ኢንዱስትሪዎች የመገንባት ከፍተኛ ጥረት ላይ ናቸው ሲሉ የሩሲያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ለብሪክስ ቲቪ ተናግረዋል።

በሌላ በኩል፤ የአሜሪካ የኢኮኖሚ የበላይነት እየቀነሰ መምጣቱን እና የደቡባዊው ዓለም ኃይሎች መነሳሳትን ተከትሎ፤ ወደ 'ባለብዝሃ-ዋልታ' ሥርዓት የሚደረገው ሽግግር ለውጥ እያመጣ መሆኑን ሚኒስቴሩ ገልጸዋል።

“በርካታ ፈጣን የኢኮኖሚ ዕድገት ማዕከላት፣ የኃይል ማዕከላት፣ የፋይናንስ እና የፖለቲካ ተጽዕኖ ማዕከላት ብቅ ብለዋል፡፡ ዓለምም በድጋሚ እየተዋቀረ ነው። ይህም በፉክክር ትግል ውስጥ እያለፈ ያለ ሂደት ነው” ሲሉ አፅንዖት ሰጥተዋል፡፡

በእንግሊዘኛ ያንብቡ

ስፑትኒክ ኢትዮጵያ | መተግበሪያ | X

አዳዲስ ዜናዎች
0